03/05/2026
ምርጫው ሲመጣ እንደ እስስት የሚቀያየርና የራሱ ጎሳ በማደራጀት ወላይታን ለመከፋፈል እየጣረ ያለ ጎሰኛውና ጽንፈኛው ወ/ማሪያም ልሳኑ
ጎሰኛውና ጽንፈኛውን ወ/ማሪያም ልሳኑ ተለዋዋጭ ባህሪ ያለዉና ለአላማ ፅኑ ያለሆነ ጥቅመኛ ሰው ነው። ለአብነትም ምርጫ 2002 ጊዜ ኢሕአዴግ፣ ምርጫ 2013 ጊዜ እናት ፓርቲና ምርጫ 2018 ዎሕነን ይዞ የመጣ የአቋምና አላማ ፅናት ችግር ያለበት ወላዋይ ሰው የምንለው በምክንያት ነው። ቀጣይ 2022 በለላ አድስ ፓርቲ ይዞ እንደሚመጣ ጥርጥር የለውም።
ግለሰቡ በዚህ በሰለጠነ ዘመን ዘዉዳዊ የሆነ የጎሳ ዳይናሲቲ ለማቋቋም በዳሞት ጋሌና መላዉ ወላይታ የሱ ጎሳ በስፋት ባለባቸዉ ቀጠና ጭምር ዞሮ በመቀስቀስ እና ማደረጃት እኔን ፓርላማ አስገቡኝ ብሎ እየለመነ ይገኛል።
በለላ በኩል ማላና ዶጎላ ሳይሆን "የእኛ ብቻ ነው መንግስት መሆን ያለብን" በሚል ሴራ ህቡእ ቡድን ሰብሳቢ፣ ም/ስብሳቢ እና ዳባዋ ሰይሟል። ይህ አደገኛ ስለሆነ መላው የወላይታ ህዝብ መታገል አለበት።
በ2010 ዓ.ም የአገርቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ የደረሰብንን አደጋ ለማፅናናት በመጡ ጊዜ ከወላይታ ህዝብ ባህልና እሴት ወጣ ባለ መልኩ የተከበረዉን መሪ የሰደበ ሥነምግባር የጎደለውና ለሰውም ክብር የሌለው ሰው ነው።
ሌላው አደገኛው ጉዳይ ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት(አባ መላኩ) ጀምሮ ጥንታዊት ወላይታ ኦርቶዶክስ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ለማከፋፈል፣ ወላይታ ብቻዋን ሲኖዶስ ልኖር ይገባል፣ ከአዉደ ምህረት፣ ከማህሌትና ቅዳሴ የለሎች አከባቢ ሰዎች ማባረርና ሀብትን እኛ እንጠቀም በማለት የፅንፈኛ ቡድን መስርቶ እየተንቀሳቀሰ መገኘቱና ለዕጩና የቅስቀሳ ስራ እንኳን የአንድ ሀይማኖት አባላት ብቻ ያነጣጠረና የሀይማኖት እኩልነትን የማያምን ፓርቲ ያደራጀ መሆኑን ህዝቡ ማወቅ አለበት።
ሌላው ከጽንፈኛው ከህወሃት ጋራ በመሆን ተልዕኮውን በመቀበል ወላይታንና ሀገራችንን ለማተራመስ ገንዘብ ተመድቦ ለተ ቀን የሚሰራና የወደቀ የጁንታ አስተሳሰብ ተሸካሚ መሆኑና እንድሁም ምልክታቸዉም ጭምር የህወሓት ነዳፊ ንብ መሆኑንም ማሳያ ነው።