Tefe Alemayehu

Tefe Alemayehu የልቤ ደስታ ጌታ

 #ይቅርታ  #የተደረገልህን  #ጊዜ  #አስታውስ!      ከሰው ልጅ አስገራሚ ባህሪይ አንዱ ለእርሱ እንዲደረግለት ሲፈልግ መድፈሩ፣ የእርሱ ተራ ሲደርስ ደግሞ "ማፈሩ" ነው። መንገድ ተዘግቶ...
03/02/2023

#ይቅርታ #የተደረገልህን #ጊዜ #አስታውስ!
ከሰው ልጅ አስገራሚ ባህሪይ አንዱ ለእርሱ እንዲደረግለት ሲፈልግ መድፈሩ፣ የእርሱ ተራ ሲደርስ ደግሞ "ማፈሩ" ነው። መንገድ ተዘግቶብን ስንጨነቅ ያኛው ሹፌር ቆሞ እንዲያሳልፈን እንጠብቃለን። መንገድ ለቅቀን ማሳለፍ ያለብን እኛ ስንሆን እንዳላየ እንሆናለን። መለስ በልና ከልጅነትህ ጀምሮ የነበረህን ሕይወት ማስታወስ የምትችለውን ያህል ለማስታወስ ሞክር። ብዙ ጊዜ ሁለተኛ እድል፣ አንዳንዴም ከሶስተኛ እድል በላይ የተሰጠህ ሰው ነህ። ላጠፋሃቸው ጥፋቶች ሁሉ የሚገባህን አላገኘህም። ከዚህ በፊት "የእግዚአብሔርን ተው" የእርሱማ ቁጥር የለም። ቢያንስ አንድ ሰው አንድን ስህተትህን እያየ እንዳላየ፣ እያወቀ እንዳላወቀ አልፎሃል። ዛሬ ዳግሞ የአንተ ተራ ነው።

ክርስትና!አንድ ሰው  ሰዎች ከበሽታቸው እንደሚፈወሱ ስለ ሰማ፥ ወደ አንድ የወንጌል አማኝ ቤተ ክርስቲያን ሄደ። በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ገብቶ ሲቀመጥ፥ ሰባኪው በኢየሱስ ለማመን የሚፈልግ ሰው...
24/01/2023

ክርስትና!
አንድ ሰው ሰዎች ከበሽታቸው እንደሚፈወሱ ስለ ሰማ፥ ወደ አንድ የወንጌል አማኝ ቤተ ክርስቲያን ሄደ። በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ገብቶ ሲቀመጥ፥ ሰባኪው በኢየሱስ ለማመን የሚፈልግ ሰው ከኃጢአቱ መዳን ብቻ ሳይሆን ከየትኛውም በሽታ እንደሚፈወስና ቁሳዊ በረከቶችን እንደሚያገኝ ሲናገር ሰማ። ይህ ሰው፣ “ይሄ ጥሩ ዜና ነው። አምናለሁ ብዬ እነግራቸውና ለቀሪ ዘመኔ ጥሩ ሕይወት የምኖርበትን ዕድል አገኛለሁ። ሀብታምም እሆናለሁ” ሲል ብዙም ሳይቆይ ሰውዬው ታመመ። በዚህ ጊዜ፣ "አንተ በሽታ፣ በኢየሱስ ስም ከእኔ ራቅ" እያለ ያዝዝ ጀመር። ነገር ግን በሽታው ሊለቅቀው አልቻለም። በመጨረሻም ወደ ሐኪም ቤት ሲሄድ ሐኪሞቹ ሊረዱት እንደማይችሉ ገለጹለት። ያለችውን አነስተኛ ገንዘብ ለቃቅሞ መድኃኒት ለመግዛት ሞከረ። የኋላ ኋላ ልቡ በብስጭት በመሞላቱ፣ "ኢየሱስ ከበሽታዬ ሊፈውሰኝና ሀብታም ሊያደርገኝ ካልቻለ፣ ለምን አምነዋለሁ?" ሲል ጠየቀ። በዚህ ጊዜ እምነቱን ትቶ፥ ወደ ጠንቋዮች ሄደ።
ስለ ክርስትና ሰዎች ከሚናገሩት ነገር ውስጥ አንዱ፥ ክርስትና የበረከት መንገድ ነው የሚለው የተሳሳተ አመለካከት ነው። ለእነዚህ ሰዎች ክርስትና እንደ ቁሳዊ ሀብት፣ ጤና፣ ከስደት ነፃ መሆን፣ የመሳሰሉት ማለት ነው። ለመሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረው ይህንን ነው? በአንድ ጊዜ ቤተሰቡን፣ ሀብቱንና ጤንነቱን ምንም ባላወቀበት ምክንያት ላጣው ኢዮብ የበረከት መንገድ ነበር? እግዚአብሔር የተስፋ ቃሉን ይፈጽምለት ዘንድ ከ20 ዓመት በላይ ለጠበቀው አብርሃም፣ ብዙ ዓመት በስደት ለኖረው ዳዊት፣ ከመደህየታቸው የተነሣ በሌሎች እርዳታ ለመኖር ለተገደዱት ኤልያስና ኤልሳዕ፣ እንደ እስረኛ ለወራት በጉድጓድ ውስጥ ለኖረው ኤርምያስ፣ ለሁለት በመጋዝ ተሰንጥቆ ለተገደለው ኢሳይያስ፣ ለወንጌሉ ሲሉ ሕይወታቸውን ላጡት ደቀ መዛሙርት ክርስትና የበረከት መንገድ ነበርን? የጳውሎስን ሕይወት በረከት በ2ኛ ቆሮንቶስ 11፡23-29 ላይ አንብብ! ከድህነቱ የተነሣ የሚተኛበት አልጋ ላልነበረውና በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሥቃይ ለተቀበለው ክርስቶስ የበረከት መንገድ ነበርን? እግዚአብሔር ሙሉ ጤና፥ በቀላሉ አልጋ ባልጋ የሆነ ሕይወት፣ ወይም ስደት የሌለበት ኑር እንደምንኖር ቃል አልገባልንም። ጤነኞችም ሆንን በሽተኞች፣ ድሆችም ሆንን ሀብታሞች ሊያበረታታን የሚገባው በመከራ መንገድ እርሱን መከተላችን ነው። በዘላለማዊ ቤት እነዚህ ምድራዊ ችግሮች ይወገዳሉ።===ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ይላል "ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን፤ የክብሩ ተካፋዮች እንሆን ዘንድ በእርግጥ የመከራው ተካፋዮች ብንሆን፥ የእግዚአብሔር ወራሾች፥ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።--የአሁኑ ዘመን ሥቃያችን ወደ ፊት ሊገለጥ ካለው ለእኛ ከጠበቀልን ክብር ጋር ስነጻጸር ምንም እንዳይደለ እቆጥራለሁ" ሮሜ 8፥17-18(አዲሱ መ.ት)።
ጳውሎስና በርናባስም፦ "የደቀ መዝሙርቱን ልብ በማበረታታትና በእምነታቸው ጸንተው እንዲኖሩ በመምከር፥ "ወደእግዚአብሔር መንግሥት ለመግባት በብዙ መከራ ማለፍ አለብን" አሏቸው። ሐዋርያት 14፥22(አዲሱ መ.ት)።
እንደገናም ሐዋርያው ጳውሎስ፦ "ክርስቶስንና የትንሣኤውን ኀይል እንዳውቅ፥በሥቃዩ ተካፋይ እንድሆንና በሞቱም እርሱን እንድመስል እመኛለሁ፤" ፊል.3፥10 (አዲሱ መ.ት)።
"ይህን ተረድቻለሁ፤ሞትም ይሁን ሕይወት፣መላአክትም ይሁኑ አጋንንት፣ያለውም ይሁን የሚመጣው፣ወይም ማንኛውም ኀይል፣ ከፍታም ይሁን ጥልቀት፣ወይም የትኛውም ፍጥረት፤በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካለው ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን አይችልም።" ሮሜ 8፥38-39(አዲሱ መ.ት)።

23/08/2022

Address

Addis Ababa

Telephone

+251912323651

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tefe Alemayehu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share