Tofik esmael

Tofik esmael እኩልነት እንዱኖር መልፈት።

25/04/2026

ጃሉድ አወል
—————-/
ቃሊቲ 08 አካባቢ ከ25 ዓመታት በፊት በ ሃሩን አረሽድ መድረሳ ቁርአን ቀርቷል ።ከስር የተቀመጠው ፎቶ ግራፍ ከጃሉድ ጋር ቁርአን የቀሩ የዛ ዘመን ደረሶች ሲሆኑ በመካከላቸው የቁርአን አቅሪያቸው ሸኽ ዳውድ ይገኙበታል።

ቃሲም አህመድ ፣አሊ በሻህ፣ አህመድ ኑር ከጃሉድ ጋር ቁርአን ቤት የተመላለሱ ብቻም ሳይሆኑ ለኢድ እና መሰል ፕሮግራሞች ግጥም እና ኢስላሚክ ድራማዎችን በመፃፍ በተማሪዎች አስርተው ለመሃበረሰቡ ዳእዋን በጥበብ የሚያደርሱ ነበሩ።

ጃሉድ በተለይ ደሞ በግጥም ስራው ዝነኛ እንደነበረ የሚያውቁት ነግረውኛል።

አባቱ ጋሽ አወል ይባላሉ የ እናቱን ስም አላገኘሁም ጋሽ አወል አነስተኛ ሻይ ቤት በዛው በ08 አካባቢ ነበራቸው እጅግ ትሁት እና ደግ ሰው ነበሩ።

ሙሃባ አወል ፣ ሃሰን አወል ፣ ደግሞ ወደአኸራ የሄደች ሙና አወል አላህ ይማራት ወንድም እና እህቶቹ ናቸው።

ህንዶች ግቢ ትምህርት ቤት ኢለመንተሪ የቀድሞው ቱሊዲምቱ የአሁኑ ደራርቱ ቱሉ ሃይስኩል ትምህርት ቤት የተማረባቸው ናቸው

ወድማችን ጃሉድ በ ኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ዘምቶ የነበረ ሲሆን በጅቡቲ ሚኒልክ ሆቴል የሙዚቃ ስራን ለተወሰነ ዓመታት ሰርቷል።

ጃሉድ አሁንም በረመዳን ወር እንደሚፆም በሚሰራው ስራ እንደሚፀፀት አሁንም በቅርቡ ያሉ ወገኖች ነግረውኛል ። ወንድሜ ጃሉድ በ እርግጥም አላህ ይወድሃል ።

በዚህ ፎቶግራፍ ውስጥ ያላችሁ የጃሉድ አብሮ አደጎች ብትደውሉልኝ ደስ ይለኛል 0911229537 ስልኬ ነው ዋትሳፕ እና ቴሌግራም መጠቀም ይችላሉ ስለምትደውሉ አመሰግናለሁ።

25/04/2026

ከተራራው ጫፍ ደርሰናል።
********************
ሰባት አመት ጠንካራ መሰረት ጥለናል።
የስራችንን ፍሬ በከፊል ለማየት ከ7ኛው ምርጫ ደጃፍ ተቃርበናል።
የነጻነት እና እኩልነት አርማን ከፍ አድርገን ለማውለብለብ በቀሩን ጥቂት ቀናት በርትተን እንሰራለን!!

ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍትህ፣ በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ከፍ ብሎ ይውለብለብ!!
ብዕር ያሸንፋል።

24/04/2026

የአክሱም ሙስሊሞችና የጽዮን ማርያም ቆይታዬ
📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶📶
በአሕመዲን ጀበል
💥💥💥💥💥

ከ16 ዓመታት በፊት በአክሱም ከተማ ያደረግኩትን ጉብኝት መሠረት በማድረግ ትዝብቴን በሚያዚያ 2002 ዓ.ል በ "የሙስሊሞች ጉዳይ" መጽሔት ላይ የጉዞ ማስታወሻዬን አስነብቤ ነበር።

ዛሬ በአክሱም ከተማ በሙስሊም አክሱማውያን ላይ የሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች፣ የሃይማኖት ጭቆናና የመብት ረገጣ፤ በጥቅሉ በመዋቅር የተደገፈው አፓርታይዳዊ መገለልና መድሎ ዛሬ የተጀመረ አይደለም። የዛሬ 16 ዓመቱ ትዝብቴ በጉዳዩ ላይ ለግንዛቤ ይረዳል ብዬ ስላመንኩ በድጋሚ ላካፍላችሁ ወደድኩ።

በወቅቱ በአክሱም ሙዚየም ውስጥ ያየኋቸው የነገሥታቱ ድንቅ ቅርሶች አስደምመውኝ ቢሆንም፤ በሌላ በኩል ደግሞ በሙስሊሞች ላይ የሚፈጸመው የተቀነባበረ አፓርታይዳዊ ጭቆና እንዳይጋለጥ የክልሉ የደህንነት መዋቅር መረጃ እንዳይወጣ የሚያደርገውን ከፍተኛ ጥረት ታዝቤያለሁ።

የጉዞ ማስታወሻዬ ረጅም በመሆኑ፣ በአክሱም የነበረኝን ቆይታ የሚገልጸውን ክፍል በ2002 እንደታተመው ያለምንም እርማት እንደሚከተለው አጋርቻችኋለሁ።

መልካም ንባብ!

❗ መልዕክቱ ለሁሉም እንዲሰርስ በሁሉም መንገድ ያጋሩ (Share)። የፌስቡክ ገጼ ቋሚ ተከታይ ያልሆናችሁ Follow በማድረግና በጽሁፉ ላይ ያለዎትን አስተያየት በ Like እና በ Comment ያጋሩ።

ጉዞ ወደ ትግራይ
💢💢💢💢💢

በኢትዮጵያ አየር መንገድ በበረራ ቁጥር 100 ወደ መቀሌ ለመብረር አውሮፕላኑ ውስጥ ተቀምጫለሁ፡፡የመብረሪያው ጊዜ 12፡30 ደረሰና ቀበቶ እንድናስር ተመከርን፡፡ስለበረራ ደህንነት ምክርም ተሰጠን፡፡፡አብራሪው በአንድ ሰዓት ውስጥ መቀሌ እንደምገባ ነገረን፡፡‹ቁርስ እዚያ እንበላለን› ሲል በአንድ ሰዓት ውስጥ መቀሌ እንደምገባ ነገረን፡፡ቁርስ እዚያ እንበላለን ብለን አስበናል፡፡ ሆኖም በረራ ሳንጀምር ተጨማሪ 15 ደቂቃ ቆየን፡፡

አብራሪው ከክፍሉ ሆኖ አውሮፕላኑ ችግር ስለገጠመው ከይቅርታ ጋር እንድንወርድ ነገረን፡፡ወረድን፡፡ሰዉ እያጉረመረመና እየተናደደ አንድ የአየር መንገዱን ሠራተኛ ምን ማድረግ እንዳለበት በጋራ ጠየቀ፡፡“አሁን ይሠራል ጠብቁ!” ሲል በትህትና መለሰ፡፡ ለአንድ ሰዓት ጠበቅን፡፡መቀሌ የተነየተው ቁርስ እዚሁ ሊሆን ግድ ሆነ፡፡ አንድ ኬክና ለሰላሳ በመብላት ጥበቃችንን ቀጠልን።

ወደ አውሮፕላኑ “ግቡ” ተባልንና ወደ አውሮፕላኑ ተቃረብን፡፡አንድ ሌላ ቴክኒሻን ነው መሰል መጥቶ “ተመለሱ ተሰርቶ አላለቀም” አለን፡፡ሰው ይበልጥ ተናደደ፡፡ግለሰቡን በቁጣ ብዙዎች ተናገሩት፡፡ህንዳውያኑ ግለሰቡ ላይ ይበልጥ ተናደው ፕሮግራማቸው እንደተስተጓበላባቸው ተናገሩ።

ሌሎች ደግሞ “በዚህ አውሮፕላንስ አንሄድም” አሉ፡፡አስራ አንድ ቱርካውያን ወንዶችና ሴቶች “ይቅርብን” ብለው ተመለሱ፡፡ ቁጭ ብለን ስንጠብቅ የተዋወቅሁትን አንደኛውን ቱርካዊ ጠየቅሁት፡፡“እቅዳችን የነጃሺን ቀብር ልንጎበኝ ነበር፡፡ጠዋት ሁለት ሰዓት መቀሌ ገብተን፣ወደ ውቅሮ በመሄድ ነጃሺን ጎብኝተን በ11 ሰዓቱ በረራ ወደ አዲስ አበባ ልንመለስ ነበር፡፡ ከዚያም ዛሬውኑ ማታ በ5 ሰዓት ላይ ደግሞ ወደ ሀገራችን ልንበር ነበር እቅዳችን፡፡ባለመዘየሬ አዝናለሁ፡፡” አለኝ፡፡ነፃ ህክምና ሊሰጡ እንደመጡም ነገረኝ፡፡

የነጃሺን ቀብር ሳይዘይር ወደ ሀገሩ ሊመለስ በመሆኑ ከፊቱ ላይ ያየሁትን ሀዘን እና የፕሮግራም አያያዛቸው እያስገረመኝ ጥበቃዬን ቀጠልኩ፡፡እነርሱ ትተው ሄደዋል፡፡ለአራት ሰዓት ሩብ ጉዳይ ላይ ተጠርተን በአውሮፕላኑ ውስጥ ገባን፡፡ ተበላሽቶ የነበረው አውሮፕላን ራሱ በመሆኑ ሰው ዱዓ ሲያደርግ(ሲፀልይ) ይስተዋላል፡፡ሆኖም ያለምንም ችግር በረራ ጀመርን፡፡በአውሮፕላን ውስጥ ሞባይል መዝጋት ግዴታ እንደሆነ ተነግሮን ነበር፡፡ነገር ግን ብዙም ሳንርቅ የአንዲት ወይዘሮ ሞባይል ጮኾ፡፡ ሴትየዋ “ተነስተናል” ብለው በመናገራቸው ሆስቴሴቹ ሮጠው አስዘጓቸው፡፡የውጭ ዜጎች ተቆጡ፡፡ምክንያቱም ሞባይል ከአውሮፕላኑ የበረራ ሥርዓት ላይ ችግር ሊፈጠር ስለሚችል ነበር፡፡

በ5 ሰዓት ላይ መቀሌ አሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ ደረስን፡፡ወረድን፡፡ንፋሱ ጠንከር ያለ ነበር፡፡አልጋ ያዝኩ፡፡መቀሌን ዞርዞር ብዬ መጎብኘት ጀመርኩ።

ጉዞ ወደ አክሱም
🔥🔥🔥🔥🔥

(በመቀሌና ነጋሽ መንደር ለቀናት ካሳለፍኩ በኋላ ወደ አክሱም ጉዞ ጀመርኩ።)
🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒🎒

ከመቀሌ መናሐሪያ ሌሊት መኪና በመሳፈር ጉዞዬን ወደ አክሱም ቀጠልኩ፡፡250 ኪሎ ሜትሩን በምን ያህል ጊዜ እንደምደርስ እያሰብኩ ጉዞዬን ቀጠልኩ፡፡ መንገዱ ተራራ ይበዘዋል፡፡ ግራና ቀኙም ገደልና ተራራ ብቻ ነው፡፡አዲግራት ገባን፡፡ቁርስ በልተን ቀጠልን፡፡ ለአከባቢ አዲስ ስለ ነበርኩ አብረውኝ የተቀመጡትን የየቦታ ስም እየጠየቅኩ አሰላቸኋቸው፡፡

አድዋ ከተማ ገባን፡፡ “ጠቅላይ ሚኒስተር መለስ የተወለደበትና ያደገበት እዚህ ጋር ነው” ብለው አሳዩኝ፡፡የአድዋ ጦርነት የተካሄደበትን ስፍራ አሳዩኝ፡፡መንገዴን ቀጠልኩ፡፡ መንገዱ ከአድዋ አክሱም አስፋልት አይደለም፡፡ግና ከአዲግራት እየተሰራ አድዋ መድረሱን አይቻለሁ፡፡ምናልባትም ይህኛው በቅርቡ እንደሚሰራ እያሰብኩ ኮረኮንቹ እያዘለለን ጉዟችን ቀጠልን፡፡አክሱም ገባን።

በ4ኪሌ ጊቢ አብሮኝ የተማረውንና አሁን በአክሱም ዩኒቨርሲቲ መምህር ወደሆነው ወዳጄ ደወልኩ፡፡አገኘሁት እርሱ ጋር አረፍኩ፡፡ሻወር ወሰድኩና ለመጎብኘት ተነሣሁ፡፡የአክሱም ሐውልት አየሁት፡፡ከጣሊያን የተመለሰውንም፣ ውድቅ የተሰባበረውን ተዟዙሬ ጎበ።

አሕመዲን ጀበል በአክሱም ጽዮን ማርያም
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

አስጎብኚው አቶ ሹሜ ብርሃነ ገለፃ አደረጉልኝ፡፡ሙዚያሙንም ከሚገባ ተመለከትኩ፡፡ከአክሱም ሀውልት አጠገብ “ታሪካዊቷ” የፅዩን ማርያም ቤተክርስቲያን ትገኛለች፡፡

አላህ ለነቢ ሙሳ የሰጠው “ታቡት” (የእነርሱ የሙሴ ጽላት የሚሉት) በዚህ ቤተክርስቲያን ይገኛል ብላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ትናገራለች፡፡ ግና በርካታ ሙሁራንን ማሳመን ቢሳናትም ቅሉ፡፡ለመኖሩም “አለ” እንጂ ገብቶ ያየ የለም፡፡ ግና ቤተክርስቲያኒቷን መጎብኘት አለብኝ ብዬ ወደ ግቢው ዘለቅሁ፡፡

ለመጎብኘት ኢትዮጵያዊ 20 ብር ይከፍላል፡፡የውጭ ዜጋ ደግሞ መቶ ሀያ ብር፡፡በአስጎብኚው መዘምር ኮከብ ሳዶአቅ ገለፃ ተጀመረ፡፡

ቤተክርስቲያኑ በታሪካዊ እንደሆነ፤ረጅም እድሜ እንዳላት በዮዲት ጉዲት እና አህመድ ግራኝ እንደተቃጠለ ተረከልኝ፡፡ኢማም አህመድ(ግራኝ) አቃጠለው የሚባለውን አሳየኝ፡፡ ከዚያ በኋላ አሁን ጽላቱ ያለበት በአፄ ፋሲለደስ እንደተሠራ ሴቶች መግባት እንደማይፈቀድላቸው አብራራልኝ፡፡ወደ ቤተክርስቲያኗ ሙዚየም ገባን፡፡በር ላይ በኤሌክትሮኒክ መሳሪያ ተፈተሽኩ፡፡ ውስጥ የተለያዩ አፄዎች ያሰሯቸው በርካታ የወርቅ መስቀሎች ይገኛሉ፡፡

የንግስት የዘውዲቱ የወርቅ ልብስና የወርቅ ዘውድ፣የአቡነ ሰላማ የወርቅ ዘውድ፣የራስ ስዩም መንገሻ የወርቅ ፀናጽል፣ የአፄ ሐይለስላሴ የወርቅ ጋሻና ጦር፣የአልማዝ ዘውድ፣የወርቅ ጫማ እና የወርቅ ጥላ ይገኛል፡፡የነገስታቱ የወርቅ ኮርቻ፣የአፄ ዘርዓ ያዕቆብ በወርቅ የተለበጠ መጽሐፍ ቅዱስ፤የአፄ ዮሐንስ የወርቅ ልብስና ዘውድ ፣እንዲሁም ባለ 13 ኪሎ ግራም የወርቅ መጽሐፍ ቅዱስ እና ሌሎችም በርካታ የቤተክህነትና የነገስታት መገልገያዎችን አየሁ።

አስጎብኚዬ “በደንብ ነው ያስጎበኘሁህ” አይነት ንግግር እየደጋገመ ጉርሻ የመፈለግ አዝማሚያ ደጋገመ፡፡ ትልቁ የወርቅ መስቀል ጋር ስንደርስ ‹‹… ተባርከህ እንድትሄድ ለበረከቱ ትንሽ ያዝ፤የወርቅ መስቀሉን በመያዝህ እድለኛነህ፡፡አየህ ወርቅ ነው፡፡ከባድ ነው፡፡” አለኝ፡፡የሳይኮሎጂ ጫወታ መሆኑ ነው፡፡ ሙስሊም መሆኔን አላወቅ መሰል “አልነካም ብልስ…” ብዬ አሰብኩ፡፡ በውስጤ ‹‹አኡዙ ቢላሂ ሚነሸይጧኒ ረጂም›› ብዩ ነካሁት፡፡

""የሙሴ ጽላት''ን አንተ አይተኻል?"
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

የውስጥ ጉብኝቴን ጨርሼ ወደ ጊቢው ወጣሁ፡፡ አስጎብኚው ቀጠሎና “ማርያም ጽዮን ገዳም ሴቶች አይገቡም፡፡ አፄ ሐይለ ስላሴ ለወንድና ለሴት ብለው በ1957 ይህን አሰሩ፡፡” ብሎ በዚያው በጊቢ ውስጥ የተሠራውን ሌላ ቤተክርስቲያን ጠቆመኝ፡፡

“አንድ ሞኒክሴ ብቻ ነው የሚገባው፤ማንም ሰው አይገባም፤ጳጳስ እንኳ አይገባም፡፡ሞነክሴው የበቃ ሰው ነው፡፡ እስከ እድሜው ልክ እዚያው ፀሎት ያደርጋል፡፡ ወደዚህ አይወጣም፡፡በቀን አንዴ ለምግብ ብቻ በዚያ አጥር ውስጥ ብቅ ይላል” እያለ ገለፃውን ቀጠለ፡፡

ጥያቄ አለኝ አልኩና “ይህ በጽዮን ማርያም ሴቶች እንዳይገቡ የያዛችሁት ህግ ከቀኖና መፃህፍት ነው ወይንስ ከመጽሐፍ ቅዱስ?” ስል ጠየቅሁ፡፡ “ምክንያቱም ሙሴ ብቻ ነው ጽላቱን የተቀበለው፡፡ በደብረሲና ገዳም፡፡

ሙሴ ብቻ ስለተቀበለው ገባዳም በተባለ ሁሉ ከዚያ ተይዞ የባህታውያን ቦታ ስለሆነ ከጄነሬሽን ጄነሬሽን (ሴቶች አይገቡም) ከሙሴ የመጣ ነው፡፡” ብሎ መለሰልኝ፡፡ “ምሁራን ይህ የሙሴ ጽላት እዚህ ናት የሚለውን አባባል አይቀበሉም፤ አለ ብቻ በማለት ለሚያነሱት ጥያቄ እንዴት ምላሽ መስጠት ይቻላል?” ስል ጠየቅሁት፡፡

እንደዚህ ሲል መለሰ “መልሳችን የሙሴ ፅላት በኢትዮጵያ ራሷ ፈቅዳ ነው የመጣችው፡፡እዚህ አክሱም ነው የምትገኘው፡፡ ምክንያቱም ዝናብ ከጠፋ የአክሱም ህዝብ ተሰብስቦ ፀሎት ሲደረግ ዝናብ ወዲያው ይመጣል፣ጦርነት ወዲያው ይቀዘቅዛል፡፡ብዙ ተዓምራት እያደረገ እዚህ ነው ያለው፡፡” አለኝ፡፡

የሙሴ ጽላትን ጠባቂ ናቸው የሚባሉትን መነኩሴ ማግኘት እችላለሁን?
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

“ውስጥ ያለውን ሞነክሴ ለምግብ ሲወጣ ጠብቄ ኢንተርቪው ላድርግለት ይፈቀዳልን?” ስል ጠየቅሁት፡፡ “አይቻልም” አለኝ፡፡ “እዚህ ስለመኖሩ በተናገርከው ላይ የሰጠኸኝ ማስረጃ ያው ‹‹አለ ነው››፡፡ ግና ይህ ንግግር ምሁራኑን ማሳመን የሚችል አይመስለኝም፡፡ ግን አንተ ራስህ አይተሃል?” ስል ጠየቅሁት፡፡ እንዳላየ ነገረኝ፡፡

እየገረመኝ አመሰገንኩና ልወጣ ስል ቆም ብሎ ሳንቲም ጠየቀኝ፡፡ “ለመግቢያ ከፍያለሁ፡፡ ላንተ ነገ እመለሳለሁ፡፡” ብዬ ልወጣ ስል ተናደደ፡፡ እኔም ይህን ያህል ቅርስ ባለበት ጊቢ እንዴት አንድም መሳሪያ የያዘ ጠባቂ ይጠፋል? ፈታሹም መፈተሻ እንጂ መሳሪያ አልያዘም፡፡ገረመኝ፡፡እያንዳንዱን የአስጎብኞዎቹን ንግግር በመቅረፀ ድምጼ አስቀርቼ የአስጎብኚው ነገር እየገረመኝ ጉብኝቴን ጨርሼ ወጣሁ፡፡


ጭቁኖቹ የአክሱም ሙስሊሞች
🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨🚨

በየጊዜው የምሰማውን የሙስሊሞችን ሮሮ ምን እንደሚመስል ለመታዘብ እየጓጓሁ ወደ ሙስሊሞች መስገጃ ሥፍራዎች ሄድኩ፡፡በከተማ መስጊድ መስራት እንደተከለከሉ ይናገራሉ፡፡ “የማርያም ሀገር ነች፣የሙሴ ጽላት አለባት፣ ታሪካዊቷ የጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን ስላለበት” መስጊድ መስራት እንደማይችሉ እንደተነገራቸው ከተራ ሙስሊሞች አንስቶ እስከ የዞኑ መጅሊስ መሪዎች ገለፃ አደረጉልኝ፡፡

በከተማው ትናንሽ ወቅፍ የተደረጉ መስገጃዎች 13 አካባቢ ይደርሳሉ፡፡እነዚህም ግለሰቦች ከመኖሪያ ቤታቸው አንዱን አልያም ሱቃቸው አንዱን ክፍል በመስገጃነት ሰጥተው ይሰገድባቸዋል፡፡ ከነዚህ ውስጥ በሺህ መሀመድ ሀጎስ ወቅፍ የተሰጠው መስገጃ ነው፡፡ሀያ ሰው አካባቢ ታሰግዳለች፡፡በራሳቸው ጊቤ ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡ሌላኛው ጁመዓ የሚሰገድበት “ሱቅ መስጊድ” የሚሉት ነው፡፡አንድ ግለሰብ እንዲሰገድበት ወቅፍ ሰጥተው ነው የሚሰገድበት፡፡ ቢበዛ 60 ሰዎችን ብታስተናግድ ነው።

ስለምትሞላ በበረንዳዋና በሱቆች መካከል ባለ ቦታ በኮሪደር ላይ ይሰገድባታል፡፡ አሰጋጅዋ ወጣት ሼህ ሙመድ አወል ያቀራል፣ ያሰግዳል፡፡ከአሊፍ እስከ ኪታቦች ያቀራል፡፡ ጠዋት ከሱብሂ በኋላና መግሪብና ኢሻ መሀል ጥቂት ሰዎችን ኪታብ ያቀራል፡፡ጠዋትና ከሰዓት ህፃናትን ቁርአን ያቀራል፡፡ ከአስር በኋላ ሴቶችን ያቀራል፡፡ የጀመዓ ሰላትንም የሚያሰግደው ራሱ ነው፡፡

የሚገርመው ሙሉ ቀን እንደዚያ እየታገለ አካባቢው ሙስሊም አዋጥተው በወር ሦስት መቶ ብር ነው የሚከፍሉት፡፡

ዳዕዋ የተጠሙ አክሱማውያን ሙስሊሞች
✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅

ዳዕዋ ማድረግ እንደምፈልግ ፈቃድ ጠይቄ ጥቂት አደረግሁ፡፡ ሰው የዳዕዋ ጥማት እንዳለው ይታያል፡፡ ኢስላምን ሲወዱ ለጉድ ነው፡፡ አንድ አባት እያለቀሱ መጥተው እጄን ሳሙኝ፡፡ “ህዝቡ ጃሂል ነው ምን ያውቃል እባካችሁ ኑና አስተምሩን! ከቻልክ በመግሪብና ኢሻም መሀል ድገም” አሉኝ፡፡

ሰው በሰልፍ እጄን ሊስም ተሰባሰበ፡፡ሳላስበው ለዝየራ መከበቤ አስገረመኝም አስደነገጠኝም፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ገጥሞኝም አያውቅም፡፡

በመግሪብና ኢሻ መሀልም ዳዕዋ አደረግኩ፡፡ ከቅድሙ ሰው ሞልቷል፡፡ ከዩኒቨርስቲ ጥቂት ተማሪዎችም ነበሩ፡፡ከሶላት በኋላ ስላሉበት አስደንጋጭና አሳዛኝ ሁኔታ ሲነግሩኝ ወላሂ ሆዴን በላኝ፡፡

ከሱብሂ በኋላ በሼህ መሀመድ ሀጎስ ወቅፍ ወደተደረገው መስጊድ አመራሁ አምስት ሰዎች ኪታብ ይቀራሉ፡፡ሽማግሌዎች ደግሞ ዱዓ ያደርጋሉ፡፡ የዞኑ መጅሊስ ፀሐፊ ሼህ መሀመድ ሀሰንም ከዚህ አሉ፡፡ስለ አክሱም ሙስሊሞች አሳዛኝና አሳማሚ ችግር ተረኩልኝ፡፡ በሀገሪቷ ህገመንግስት ቢኖርም መብት ብሎ ነገር ማግኘት እንዳልቻሉ ነገሩኝ፡፡ቤተክህነት ብዙ ጫና እንደምታስደርግባቸው ተረኩልኝ፡፡

የአክሱም ከተማ ሙስሊም ብዛቱ አስራ አምስት ሺ እንደሚደርስ ነገሩኝ፡፡እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ2005 የስታክስቲክስ ባለስልጣን ያወጣው መጽሐፍ የአክሱም ህዝብ 47,320 እንደሆነ ይተርካል፡፡ከዚህ ውስጥ የኦርቶዶክስ ክርስቲያን የሆነው 75% (35,490) እንደሆነ ይናገራል፡፡በደጋ ሀሙስ ሰፈር ወይዘሮ ሸምሲያ ሼህ ሷሊህ የኢቢዩ ሕጻናትን ቁርአን እንደሚያቀሩ ወዳጄ ተረከልኝ፡፡


ከ120 በላይ ሕጻናትን ቁርአን እንደሚያቀሩና ተማሪዎቹ በወይዘሮዋ(ዑስታዝዋ) ቤት ዉስጥ የራሳቸውን ቁርአንንና ወንበር ይዘው እንደሚመጡ ሰማሁ፡፡ ከደርግ ዘመን በፊት ሙስሊሙ መሬት መያዝ እንደማይችልና ቤት እንደሌለው ሽማግዎች ተረኩልኝ፡፡

ደርግና የየአክሱም ሙስሊሞች
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

በአክሱም መስሊሙ ቤት ሊይዝ የታቻለው በደርግ ዘመን እንደሆነ አብራሩልኝ፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ሙስሊሙ መሬትም ቤትም እንዳይኖረው ይቃወሙ የነበሩትን የቤተክህነት ቀሳውስትን በወቅቱ ይፈራ የነበረው የደርጉ መሪ አፈወርቅ አለምሰገድ ጠራቸው፡፡

ለሙስሊሙ የቤት መስሪያ ቦታ ቢሰጣቸው ይቃወሙ እንደሆነ ጠየቃቸው፡፡ በጣም ይፈራ ስለነበር እንደማይቃወሙ ገለጹለት፡፡ “ብትቃወሙ ኖሮ በአደባባይ ነበር የምሰቅላችሁ” ሲል ተናገራቸው፡፡ከዚያም ሙስሊሙ በ30 ብር መሬት መራላቸው፡፡ ከዚያም መሬት መያዝ ቻሉ፡፡ የንግድ ቦታውን ደግሞ ጣሊያን ነበር ለሙስሊሞች የሰጠው፡፡

መረጃ እንዲወጣ ስለማይፈልጉ ይይዙሃል
ቶሎ ከአክሱም ዉጣ።
📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕📕

አሳዛኙን የአክሱም አሳዛኝ ቅኝቴን ጨረስኩ፡፡በአንድ መስገጃ ቦታ ሳለሁ አንድ አባት መጡና “ቶሎ ከአክሱም ውጣ፣በኋላ ይይዙሃል፣መረጃ እንድታወጣ አይፈልጉም” አሉኝ፡፡

የበረራ ሰዓቴ ስለደረሰ ወደ አፄ ዩሐንስ 4ኛ አየር ማረፊያ በባጃጅ አመራሁ፡፡አውሮፕላኑ የሚነሳው 2፡50 ነበር፡፡እቃዎቼን አስፈትሽ ጀመር፡፡ሁሉንም ከፍተው አዩ፡፡ወክማንና ካሴቶች አየችና ፈታሽዋ፡፡ ወክማኑን አወጣች፡፡ “ምንድ ነው?” ስትል ጠየቀችኝ፡፡ ለጉብኝት እንደመጣሁ ነገርኳት፡፡ ወክማኑን ከፈተችው፡፡በሁሉም ቦታ ስጎበኝ በወክማን እየቀዳሁ ነበርና እንዳጋጣሚ ሆኖ የአክሱም ሀውልት ጉብኝቴ ግዚ የተቀዳው ሆነ፡፡ገባሁና መጠበቅ ጀመርኩ፡፡

በአየር ማረፊያው የሚሸጠው በጠቅላላ የቤተክርስቲያን መገልገያዎች ናቸው፡፡በአንድ ጎን ላይ ተምርና ማር አየሁ፡፡ ተምሩ የደረቀ ነው የታሸገውን በ10 ብር ገዛሁ፡፡ ማሩ ግን በጣም ነጭና ወተት የመስለ ነበር፡፡ ኪሎወን በ70 ብር ገዛሁና ጥበቃዬን ቀጠልኩ፡፡
2፡50 አለፈ፡፡

አንድ የአየር ማረፊያው ደህንነት መጣና ‹‹ውስጥ ትፈለጋለህ!›› አለኝ፡፡ወደ ውስጥ ገባሁ፡፡ውስጥ ያለው ሀላፊ “በኤክስረይ ስናየው ሻንጣህን ደግመን መፈተሸ እንዳለብን ስለተሰማን ነው፡፡ይቅርታ፡፡ሻንጣህን ክፈት” አለኝ፡፡

ግርም አለኝና ያቺ ወክማን ደግሞ ልትደመጥ ነው ብዬ በልቤ አሰብኩ፡፡ሁሉንም አወጡና በጥንቃቄ ፈተሹ፡፡አመስግነው መለሱኝ፡፡

አዲስ አበባ እንደርስበት የነበረው ሰዓት ሁላ አለፈ፡፡አንዲት ትንሽ አውሮፕላን መጣች፡፡ጥቂት ሰዎች ተጠርተው ገቡ፡፡የኛ ቦይንጉ ስለሆነ እንድንጠብቅ ተነገረን፡፡ ለ5 እስር ጉዳይ ላይ መጣ፡፡ግማሽ ሰዎችን ከጎንደር ጭኗል፡፡በረራ ወደ አዲስ አበባ ጀመርን።

24/04/2026

ወይዘሮ አዜብ ያኔ የሀገሪቱ ቀዳማዊት እመቤት በነበሩ ሠዓት በውስጥ ጫና ወራቤ ላይ ቤተክርስቲያን እንዲሠራ አደረጉ። ይህንን ሲያደርጉ ወራቤ ውስጥ አንድም ተወላጅ ክርስቲያን ያልነበረ መሆኑን ልብ ይሏል! ነገር ግን ይህንን በሚያደርጉበት ሠዓት ተጋሩ ወንድምና እህቶቻቸው በተወለዱበት ከተማ የመቀበርና መስጂድ የመገንባት መብታቸው ሲነፈግ አንዳች አልፈየዱም። ይህ በሚሆንባት ሀገር ውስጥ ስለአክሱም ሙስሊም አንተን ምን ያገባሀል የሚል መኖሩ ደግሞ ይገርማል። በተለይ ለእንደኔ ዓይነቱ ስልጤ ሙስሊም ስለአክሱማውያን ሙስሊሞች መብት የማውራት መብት ብቻ ሳይሆን ሞራላዊ አቅሙም አለው። ስለእውነቱ እናውራ ከተባለ አክሱም ለክርስትና ከምትቀርበው በላይ ስልጤ(ወራቤ) ለኢሥላም ቅርብ ናት። ከመሆኑም ጋር ብዙ አብያተ ክርስቲያናት አሉ።

✍️ Miftah Muzemil

24/04/2026

“The Power of Negotiation” የተሰኘው የአባስ አራግቺ መጽሐፍ የኒው ዮርክ ታይምስ የወቅቱ ምርጥ ሽያጭ ሆኖ ተመዘገበ‼️

የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ “The Power of Negotiation” የተሰኘው መጽሐፍ፡ የኒው ዮርክ ታይምስ የወቅቱ ምርጥ ሽያጭ ሆኖ ተመዝግቧል።

መጽሐፉ ስለ ዲፕሎማሲ፣ ስትራቴጂ እና የገሃዱ ዓለም የድርድር ስልቶች ምን እንደሚመስሉና በአለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ ድርድር ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት በሰፊው ያብራራል።

መጽሐፉ በኢራን የኒውክሌር ጉዳዮች ዙሪያ ሲካሄዱ በቆዩ የድርድር ሂደቶች ወቅት የነበሩ ልምዶችን በመቀመር ለዓለም አቀፍ ግጭቶች በሰለጠነ መንገድ እንዴት መፈታት እንዳለባቸው በርካታ ስልቶችን ይተነትናል።

በስትራቴጂካዊ መንገድ፣ በትዕግስት፣ በዝግጅት እና በጽኑ መርህ ላይ የተመሰረተ ድርድር ከፍተኛ ሃይል እንዳለው ይገልፃል።

አራግቺ የድርድር ጥንካሬ በሶስት ምሶሶዎች ላይ የተመሰረተ ነው ይላሉ፡ እነሱም፦

➔ የተደራዳሪ ሀገራት ውስጣዊ አቅም፤
➔ የዲፕሎማቶች ልምድና ችሎታ፤
➔ የስትራቴጂክ ምህዳር ናቸው።

መጽሐፉ የስትራቴጂካዊ ትዕግስትን፣ ግፊትና ጫናዎችን በመቋቋም ተረጋግቶ የማጤንን እና የጥሞና ዘዴዎችን በአግባቡ የመጠቀምን አስፈላጊነት በእጅጉ ያጎላል።

በተጨማሪም በምስራቃዊ እና በምዕራባውያን ዲፕሎማሲያዊ ስልቶች መካከል ያለውን ልዩነት እና ለስኬታማ ድርድር አስፈላጊ የሆኑ ባህሪያትንም ያጠቃልላል።

እ.ኤ.አ. ኤፕሪል 2026 ላይ የወጡ ሪፖርቶች እንደሚያመለክቱት፡ መጽሐፉ ከፍተኛ ሽያጭን ያገኘ መሆኑንና የብዙሃኑን ትኩረት የሳበ መጽሐፍ እንደሆነም ይጠቁማሉ።

24/04/2026

የአባስ አራግቺ “የድርድር ሀይል” የተሰኘው መፅሀፍ በኒውዮርክ ታይምስ ለሽያጭ ከቀረቡት ውስጥ ምርጥ መፅሀፍት ተርታ ተቀመጠ!

24/04/2026

የአልሂዳያ ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ዶርም ህንፃ 1 አሁናዊ የግንባታ ደረጃ ...

625 ካሬ ላይ ያረፈ፣ በየወለሉ 16 የተማሪዎች ማደሪያ ክፍሎች፣ በየወለሉ 10 የመፀዳጃ ክፍሎች፣ በየ ወለሉ የውዱዕ ቦታዎች፣ ...ያሉት ግዙፍ ህንፃ ሲሆን በሁለት በኩል መግቢያና መውጫ ደረጃዎች አሉት።

24/04/2026

ንጉስ ነጃሺ አክሱምና ዉቅሮ
✅✅✅✅✅✅✅✅

በአሕመዲን ጀበል፥ክፍል አንድ
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴

ይህ ጹሑፍ በትግራይ ጦርነት ጊዜ የነጃሺ መስጂድ ላይ ጥቃት በተፈጸመ ጊዜ ተጽፎ በሦስት ተከታታይ ክፍሎች በኔ በአሕመዲን ጀበል የፌስቡክ ገጽ እእና የግል ፕሮፋይል ላይ በጃኑዋሪ 2፥ 2021 ተለጥፎ ነበር። ዛሬም በድጋሚ ሦስቱ ክፍሎች በተከታታይ ይቀርባል። መልካም ንባብ።

🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁🎁

ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) በእምነት ነጻነት፣ እጦት ጭቆናና መከራ ከባልደረቦቻቸው መከላከል እንደማይችሉ ሲገነዘቡ ወደ ሐበሻ ምድር እንዲሰደዱ መከሯቸው። እንዲህም አሏቸው፡-

‹‹ወደ ሐበሻ ተሰደዱ፤ በእርሷ አንድ ንጉሥ አለ። ከእርሱ ፊት ማንም ተበዳይ አይሆንም። … (ስለዚህ ተሰደዱ)፤ አላህ ካላችሁበት ሁኔታ አውጥቶ ድል እስክንጎናጸፍ ድረስ…፡፡››(ሙሐመድ ጦይብ ኢብን ሙሐመድ ኢብን ዩሱፍ፣ ኢትዮጵያ እና ኢስላም (ትርጉም)፣ ነጃሺ ማተሚያ ቤት፣ ገጽ 9)

ሰሀቦችም በሁለት ዙር ተሰደው ወደ ኢትዮጵያ-አክሱም መጡ፡፡በንጉስ ነጃሺ ዘንድ ነጻነትን ተጎናጸፉ፡፡ የነቢዩ ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) ባልደረቦች በሐበሻ የገጠማቸውን ሁኔታ እንዲህ ሲሉ መስክረዋል፡-

‹‹ሐበሻ ገባን። መልካም ጎረቤቶችንም አገኘን። በሃይማኖታችን ምክንያት የሚደረግብን ተፅእኖ አልነበረም። አላህንም በሰላም መገዛት ጀመርን። አንድም ችግርና መከራ አላጋጠመንም። የምንጠላውን ነገር አልሰማንም።››

(አህመዲን ጀበል፣ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ከ615-1700 የጭቆናና የትግል ታሪክ፣2003፣ገጽ 35)

መናገሻ ከተማውን አክሱም ከተማ አድርጎ ይመራ የነበረው ንጉስ ነጃሺ በኢስላም ኃይማኖት ታላቅ ስፍራ ከሚሰጣቸው ስብዕናዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ለሙስናና የስጦታ ድለላ ሳይታለል የእምነት ነጻነትን ጨምሮ ሙሉ ነጻነትና ጥገኝነትን ለነቢዩ ሙሐመድን(ሰ.ዐ.ወ) ባልደረቦች በመስጠቱና በኃላ ላይም ኢስላምን ተቀብሎ ኦክቶበር/ኖቬምበር 630 (ረጀብ ወር 9ኛ ዓ.ሂ.) ሲሞት የርሱን ሞት መልዓኩ ጂብሪል ሲነግራቸው ለርሱ ነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) ለሞቱ ሙስሊሞች ላይ የሚሰገደውን ሰላትን ሰግደዋል፡፡

(ኢማሙ ጦበሪ፣ ታሪኽ አል ሩሱል ወል ሙሉክ፣ ጥራዝ 3፣ ገጽ 81፤ ኢብኑ ከሲር፣ አል-ቢዳያ ወኒሃያ፣ ጥራዝ 3፣ ገጽ 99፤ ኢብኑል አሲር፣ አል-ካሚል ፊ ታሪኽ፣ ጥራዝ 1፣ ገጽ 347)

አላህም ንጉሥ ነጃሺ ኢስላምን መቀበሉን በማረጋገጥ የሚከተለውን የቁርኣን አንቀጽ አወረደ፡-

وَإِنَّ مِنْ أَهْلِ الْكِتَابِ لَمَنْ يُؤْمِنُ بِاللَّهِ وَمَا أُنْزِلَ إِلَيْكُمْ وَمَا أُنْزِلَ إِلَيْهِمْ خَاشِعِينَ لِلَّهِ لَا يَشْتَرُونَ بِآيَاتِ اللَّهِ ثَمَنًا قَلِيلًا أُولَئِكَ لَهُمْ أَجْرُهُمْ عِنْدَ رَبِّهِمْ إِنَّ اللَّهَ سَرِيعُ الْحِسَابِ (سورة : آل عمران آية: 199)

ከመጽሐፉ ሰዎች መካከል አላህን ፈሪዎች፣ በአላህ አናቅጽትም ጥቂትን ዋጋ የማይሸምቱ ሆነው በአላህ የሚያምኑ፣ ወደ እናንተ የተወረደውንም ወደነርሱ የተወረደውንም (እውነት የሚቀበሉ) ወገኖች በእርግጥ ይገኛሉ። እነርሱ ከጌታቸው ዘንድ (የላቀ) ምንዳ ተዘጋጅቶላቸዋል። አላህ ምርመራው ፈጣን ነው። (ቁርኣን፣ዓሊ ኢምራን፣ 3፡199)

(ይህ የቁርኣን ጥቅስ የወረደው በነጃሺ ምክንያት መሆኑን በርካታ የኢስላም ሊቃውንት በመጽሐፍቶቻቸው አብራርተዋል። ለምሳሌ፡- ኢብኑ ከሲር፣ ተፍሲር አል ቁርአን አል ዓዚም፣ ጥራዝ 3፣ ገጽ 199፤ ኢማሙ ጦበሪ፣ ጃሚዑል በያን፣ ጥራዝ 2፣ ገጽ 532፤ አል በገዊ፣ መዓሊም አት ተንዚል፣ ጥራዝ 2፣ ገጽ 155፤ ሲልሲለቱ ሶሒህ አል ሙኽተሰር፣ ጥራዝ 8፣ ገጽ 51፤ ኢብኑ ተይሚያህ፣ መጅሙዐቱል ፈታዋ፣ ጥራዝ 4፣ ገጽ 209፤ ተፍሲር ኢብን አቢ ሃቲም፣ ጥራዝ 3፣ ገጽ 318፤ አል-ሙዕጀም አል-አውሰጥ ሊ ጦበራኒ፣ ጥራዝ 10፣ ገጽ 357 እና ሌሎችም በርካታ መጻሕፍትን ማመልከት ይቻላል፡፡)

በዚህ ታሪኩና ማንነቱ የተነሳ የነጃሺ ስም በታሪክ ጎላ ብሎ ሰፍሯል፡፡

ዉቅሮ-ነጃሺ የሞተበት ስፍራ
📮📮📮📮📮📮📮📮

ዉቅሮ የሚገኘው የነጋሽ(ነጃሽ) ከተማ ደግሞ ንጉስ ነጃሺ የሞተበት ወይም የተገደለበት ስፍራ እንጂ የሕወሃት ሰዎች ሆነ ብለው ከአክሱምም ከነጃሺም ለመጠቀም ሲሉ እንደሰሩበት እና የመጅሊስ ሰዎችን ጨምሮ ብዙዎችም ልብ ሳይሉ እንደተከተሉት ነጃሺ መናገሻው ዉቅሮ ከተማ አልነበረም፡፡ የንጉስ ነጃሺ መናገሻ አክሱም ከተማ ነበር፡፡የነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ሰሀቦች የእምነት ነጻነት ያገኙበትም አክሱም ራሷ ነበረች፡፡

በስደት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በአክሱም ከተማ ይኖሩ ከነበሩት መካከል በኃላ ላይ በንጉስ ነጃሺ ወኪልነት ለነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) የተዳረች ዑሙ ሀቢባ አንዷ ነበረች፡፡ ዑሙ ሀቢባና ሌላኛዋ የነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ባልተቤት ኡሙ ሰለማና ኡሙ ሐቢባ (ረ.ዐ.) የአክሱም ማርያም (ጽዮን) ቤተ ክርስቲያንን ጎብኝተዋል።

በሶሂህ አል-ቡኻሪ የሐዲስ ጥራዝ ላይ በተዘገበው መሠረት በጉብኝታቸው ወቅት በቤተ ክርስቲያኒቱ የተመለከቱትን ‹‹የጻድቃን›› ምስሎች ወደ አገራቸው ከተመለሱ በኋላ ለነቢዩ ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) ነግረው ነበር። (Sahih Bukhari, Vol. 1, book 8, number 426 and Vol. 2, book 23, number 425)

እንደ የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ስርግው ሐብለ ሥላሴ ገለጻ ስለአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲን በስደት ወደ ኡሙ ሀቢባና ኡሙ ሰለማ ለነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐወ.) የገለጹበት ማስረጃ ስለቤተክሪስቲያኒቱ ዉስጣዊ ገለጻ "Elaborate and colorful description" (የተብራራና የሚያምር ገለጻ) ነው ያሉት።ፕሮፌሰር ስርግው "Ancient and Medieval Ethiopian History" በተሰኘው መጽሐፋቸው ገጽ 185 ላይ የግርጌ ማስታወሻ ቁጥር 30 ላይ ይህ አገላለጽ ቢያንስ ሁለት ጠቀሜታ እንዳለውና የአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያንን በተመለከተ የመጀመሪያው የታሪክ መረጃ መሆኑን አስረግጠው ጠቅሰዋል።

ታላቁ የቁርኣን ተንታኝ ኢማም ኢብኑ ከሲር ‹‹ተፍሲር አል-ቁርአኑል ዓዚም›› በተሰኘው የቁርኣን ማብራሪያ መጽሐፋቸው ላይ እንዳሰፈሩት ኢስላምን ከተቀበሉ በኋላ ንጉስ ነጃሺ ወደ ነቢዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ልከዋቸው የነበሩዋቸው የሀገራቸው ሰዎች ወደ ነጃሺ ተመልሰዋል። ስለ ነቢዩም (ሶ.ዐ.ወ) በዝርዝር ለነጃሺ ነግረዋል። ነጃሺ ኢስላምን ቀድሞ ቢቀበልም ከእነርሱ ከሰማ በኋላ ወደ ነቢዩ (ሶ.ዐ.ወ) ለመሄድ ጉዞ ጀምሮ ነበር። ግና ከአክሱም ከወጣ በኋላ በስደት (በጉዞ ላይ) በመንገድ ላይ ሞቷል።

(ተፍሲር አል-ቁርአኑል ዓዚም፣ ጥራዝ 3፣ ገጽ 166)

በኦክቶበር 2009 ትግራይ ውቅሮ ነጋሺ መንደር (ከመቀሌ ከተማ 65 ኪሎ ሜትር) በሄድኩበት ጊዜ የነጃሺን ቀብር ጎብኝቻለሁ። ከነጃሺ መቃብር በመቶዎች ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘው ቤተ ክርስቲያን ከነጃሺ ጋር የሚያገናኛት ታሪክ እንዳላት ሰማሁ።

በኦክቶበር 26/2009 ወደዚያው አቀናሁ። ‹‹ከዲህ ማርያም›› ቤተክርስቲያን ትሰኛለች። የቤተ ክርስቲያኒቱ ቄስ የ 75 ዓመቱ አዛውንት ቄስ ታደሰ ገብረ ሥላሴ በር ላይ ቆመው አገኘኋቸው። ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ ጠየቅኳቸው። ከስያሜው አመጣጥ ጀምረው እንዲህ ማብራራት ያዙ፡-

‹‹አንድ ሰው ወደ እስላም አገር ሊሄድ ሲል ከሚስቱ ጋር መጥቶ ነበር ይባላል። ከሚስቱ ጋር ሲሄድ ‹የት ነው የምንሄደው?› ብላ ሚስቱ ጠየቀች። ‹ወደ እስላም አገር እስልምናን ለማመን ነው የምንሄድ› ብሎ ተናገረ። ‹የት ነው የምንሄደው?› ብላ ለአሽከሮች ነገረች (ጠየቀች)፤ ‹ወደ እስልምና አገር፣ እስልምናን ለማመን ነው የምንሄድ ያለን› ብለው ነገሯት።

ከዚያ ወዲህ ‹አልሄድም› አለች፤ ቀረች። ከዚያ ባሏ ላይ (የአሁኑ የነጃሺ ቦታ) ሆኖ ጠይቋል። ‹ሚስቴ የት ሄደች?› አለ። ‹የለችም፤ አልመጣችም› አሉት። ‹ከዳች ወይ?› ብሎ ሲናገር ከዚያ በኋላ ነው እርሷ የነበረችበት ቦታ (ቤተ ክርስቲያኒቱ ያለችበት ቦታ) ከዲህ የተባለው ሲባል እንሰማለን። ከዚህ በኋላ (በመታሰቢያነት) ‹ከዲህ› ተብሎ ይጠራል።

ስለነጃሺ እንዲነግሩን ጠየቅኳቸው። ቦታውም እንዴት ‹‹ነጋሺ (ነጃሺ)›› ተብሎ እንደተሰየመም እንዲያብራሩልን ጠየቅኩኝ። ምላሻቸውን እንዲህ ሲሉ ቀጠሉ፡- ‹አይደለም። እኔ የምለው እኮ እርሱ ነው። ከሚስቱ ጋር የመጣው እርሱ ነጃሺ ነው። እርሱ ነጃሺ አደርእዝ ነው የሚባለው። እዚያ ላይ ነው ተገድሎ የሞተ ይባላል። በኋላ ነጋሺ ተብሎ ተጠራ። የርሱ ስም ነው። በንግሥና ስለመጣ ነው ነጋሺ እየተባለ የምንሰማው›› ብለው መለሱልኝ። ለተጨማሪ ጥያቄዎቼ ምላሻቸውን ቀጠሉ፡-

‹‹እርሱ ሚስቱንና አሽከሮቹን ይዞ በእስልምና ሊያምን ሲሄድ ሚስቱ ለአሽከሮቹ ጠየቀች። ‹የት ነው የምንሄድ?› ስትል፡፡ ‹ይህ ባልሽ ወደ እስልምና ለማመን ነው የሚሄደው› ብለው የነገሯት ጊዜ ‹እኔም ከዚህ አልሄድም› ብላ ከዚህ ቀረች።

እርሱም ላይ (የቀብሩ ቦታ) ነጋሺ በደረሰ ጊዜ ሌሎች ከአክሱም መጥተው ‹ወዴት ነው የሚሄደው?› ብለው ገድለውታል የሚባል ወሬ ነው የምንሰማው፡፡››

‹‹ንጉሥ ነበር?‹‹ ስል ጠየቅኳቸው። ‹‹አዎ!›› ሲሉም መለሱልኝ። ‹‹ሲሄድ ነው የተገደለው። ሊሄድ አይገባውም ብለው ነው፤ ‹ንጉሥ መስለም የለበትም› ብለው ነው ሲባል እንሰማለን…፤ እስላሞች ነጃሺ ይላሉ። እርሱ ግን አደርእዝ ነው። ‹ወደ እስልምና አገር ሄዶ ስማችንን ሊያጠፋ ነው› ብለው ገደሉት…›› ሲሉ መለሱልኝ።››

(አህመዲን ጀበል፣ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ከ615-1700 የጭቆናና የትግል ታሪክ፣2003፣ገጽ 53-54)

ሊዳፈን ያልቻለው የዉቅሮ የነጃሺ መካነ መቃብርና መስጊድ
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

የነጃሺ መቃብር አስጎብኚ እንዳብራሩልኝ በዐፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የነጃሺ መቃብር እንዳይታወቅ ይፈለግ ነበር። ቦታው እንዳይገነባ ማዕቀብ እንደተጣለበት፣ ሆኖም የዛሬ ሃምሳ ዓመት ገደማ (1946) የአድዋ ተወላጅና በወቅቱ አስመራ ይኖሩ የነበሩት ሐጂ ሙሐመድ ዐብዱ ኃይለ ሥላሴ ወደ ውጭ በሄዱበት በድብቅ በእምነበረድ አሠሩት።

ዛሬ የሐጂ ዐብዱ መቃብር በዚያው ግቢ ውስጥ ይገኛል። የንጉሥ ነጃሺ ሙሉ ስም ‹‹ዐፄ አደርእዝ አብሑር አብጀር›› እንደሆነም ገለፁልኝ።

የነጃሺና የተወሰኑ ሶሐባዎች መቃብር ላይ በግንብ ቤት ተሠርቷል። የነጃሺ መቃብር ከጥንት ጀምሮ በአካባቢው ይታወቃል። ለምሳሌ እ.ኤ.አ በ1533 ኢማም አሕመድ ኢብኑ ኢብራሂም አል-ጋዚ የአጋሜን ሹም ለማጥቃት በትግራይ በዘመቱበት ከነሠራዊታቸው የነጃሺን መቃብር ጎብኝተዋል። ዐረብ ፈቂህ ‹‹ፉቱህ አል-ሐበሻ›› በተሰኘው መጽሐፉ እንዲህ ጽፏል፡-

‹‹ከአሕመድ ነጃሺ ቀብር ዘንድ ደረሱ። የአላህ ራህመትና ሰላም ይውረድበትና እርሱ በነቢዩ ጊዜ የኖረው ነው። ‹ዛሬ ታዋቂውን አስሐማ አሕመድ አል-ነጃሺን እንዘይር። ነገ ደግሞ ወደ ትግሉ እንሄዳለን› ሲሉ ሙስሊሞች ኢማሙን (አሕመድን) ጠየቁ። ኢማሙ ‹ዛሬ በጣም አስፈላጊ (ጠቃሚ) በሆነ ዘመቻ ውስጥ ነን። ነገ እንጎብኝ› ሲል መለሰላቸው። ኢማም አሕመድ ከነፍሰጡር ባለቤታቸው ጋር በመሆን በውቅሮ የነጃሺን ቀብር ዘየሩ። የሙስሊሙ ጦርም የነጃሺን ቀብር ዘየረ። በዚያው ሳሉ የኢማሙ ሚስት ወንድ ልጅ ወለደች። የተወለደውን ልጅ (በኢትዮጵያዊው ሙስሊም መሪ ስም) ‹አሕመደል ነጃሺ›› ሲሉ ሰየሙት።››

(Shihab ad-Din Ahmad bin ‘Abd al-Qader bin Salem bin ’Utman ’Arab Faqih, Futuh al-Habaša. The Conquest of Abyssinia, Paul Lester Stenhouse (Trans.). USA. Tsehai Publishers and Distributors. 2003, Pp. 351-352)

አቶ ቡሽራ ሸኽ የህያ ‹‹የኢትዮጵያዊው ንጉሥ አሕመድ አል-ነጃሺ ታሪክ›› በተሰኘው መጽሐፋቸው ይህንን ጉዳይ አብራርተዋል። ጉዳዩ እንዲህ ነው፡-

አዝማች ሐጂ ሙሐመድ ዐብዱና ወንድሞቻቸው ለረጅም ዓመታት የንጉሡና የአስሓቦች መካነ መቃብርና መስጊዱ ዙሪያውን በድንጋይ፣ ጣራው በእንጨትና በአፈር ተሠርቶ የነበረው የተወሰነው ጎኑ እየፈራረሰ በማየታቸው ቅር ተሰኙ።

ቅርሱ ከጥፋት እንዲጠበቅና ለትውልድ እንዲተላለፍ በአዲስ መልክ ሊያስገነቡ ፈለጉ። የሥራ ፈቃድ ለማግኘት በ1945 ዓ.ል ወደ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ቤተ-መንግሥት አዲስ አበባ ድረስ ተጓዙ። የነጃሺን መቃብርና መስጊዱን ዳግም ሊያድሱ ፈቃድ ፈልገው መምጣታቸውን ለንጉሡ አማካሪ ለራስ እምሩ አማከሩ። ወደ ንጉሱ እንዲቀርቡ አደረጓቸው። ጥያቄያቸውን በጽሑፍ ለንጉሡ አቀረቡ።

ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ጉዳዩን ካደመጡ በኋላ ፈቃድ ከለከሉ። እነ አዝማች ሐጂ ሙሐመድ ዐብዱ አዝነው ወደ ትግራይ ተመለሱ። ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ፈቃድ ቢከለክሉም በኋላ ላይ የትግራይ ገዥ የነበሩት ራስ ሥዩም መንገሻ ‹በድብቅ ቀስ ብላችሁ ሥሩ› ብለው በመፍቀዳቸቸው ዳግም ታደሰ።››

(አቶ ቡሽራ ሸኽ የህያ፣ የኢትዮጵያዊው ንጉሥ አሕመድ አል-ነጃሺ ታሪክ፣ በድር ማተሚያ፣ መስከረም 2003፣ ገጽ 40-41)

ዐፄ ኃይለ ሥላሴም ወደ ግብጽ በአዝሐር ዩኒቨርሲቲ የነጃሺ መቃብር የት እንደሆነ ተጠይቀው በጭራሽ እንደማያውቁ ገልጸው ነበር። (ዐብደላ ዐብዱረሕማን ኑር፣ የዓይን ምሥክር፣ ገጽ 119)

በጥንታዊው የንጉስ ነጃሺና የሰሀቦች መካነ መቃብር ቅጥር ጊቢ ከጥንት ጀምሮ በነበረው የመስጂድ ፍርስራሽ ላይ በምስል የሚታወቀውን ዘመናዊ መስጊድ ያሰሩት ሼህ ሙሐመድ ሁሴን አላሙዲ ሲሆኑ የነጃሺን መንደርና ሙሉ ቅጥር ጊቢውን ዉብ በሆነ መልኩ ተመላልሰው ለምነው ያሰሩት ለታሪኩ ከፍተኛ ስፍራ የሚሰጡት ቱርኮች ነበሩ፡፡

በንጉስ ነጃሺ ስም በተለያዩ ሀገራት አደባባዮችና ተቋማት ሲሰየሙ ታሪኩና ቅርሱ ተገቢውን ስፍራ ባለማግኘቱ በሀገሩ በኢትዮጵያ ግን የሚገባውን ክብር አላገኘም፡፡ ስለነጃሺ መስጊድ መጠቃት መናገር ወይም መጻፍን አስመልክቶ በመቃወም ለመተቸት የሚሯሯጡትን ስታይ ‹‹የነጃሺ መስጊድስ የአክሱሙ ዱራ መስጊድ እጣ ፈንታ ይደርሰው ይሆን?›› አያስብልም?

ይቀጥላል…

24/04/2026

ይሄ ልጅ ስሙ ይባላል። የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የነበረና ከተወዳጅ ዘማሪያቸው ነበር።ግቢ እያለ ለግቢ ጴንጤ ተማሪዎች ነበር።ዛሬ ላይ ግን ክርስትና በቃኝ ብሎ ወጥቶዋል።በጣም ደስ የሚል ስብዕና ያለው ልጅ ነው።እርጋታው አለም ባንክ የሚገኘው ራሱ እንደሱ አይረጋም😊።

ልጁ Deep አንባቢ ነው።ጥልቅ አንባቢ መሆኑ ክርስትና ላይ ጥልቅ ጥያቄዎችን እንዲያነሳ አድርጎታል።ታዲያ ለጥያቄው መልስ የሚሰጠው ሳይሆን ጥያቄዎችህ ልክ ናቸው እያሉ ከክርስትና እየወጡ ያሉ ወጣቶች እየበረከቱ ነው።

ዛሬ ከቴክቶክ ሙስሊም የንፅፅር መምህራን እየተወያየ አይቼው ቀጣይ ማረፊያው እስልምና እንደሚሆን በአላህ ላይ ተስፋ አደረኩኝ።ጃቢር የሚባል ሰለምቴ ወንድማችን ከአዶኒ ጋር ተመሳሳይ ጉዞ እንደነበረውና ዛሬ ለጥያቄዎቹ መልስ አግኝቶ በእስልምና ነብሱ እርፍ እንዳለች በተዋቡ አንደበቶቹ አስረዳው።ስለ እስልምናም እንዲያጠና ጥያቄዎችንም እንዲጠይቅ ሲጋብዘው ሳይ ሁሌም እንደምለው ለእስልምና መመረጥ ምን አይነት ፀጋ ነው አልኩኝ።

I am proud to be Muslim💙

24/04/2026

፦ ኢራን በሆርሙዝ የባህር ስርጥ “የመንጋ ጥቃት” ስልትን ተግባራዊ ማድረጓ ተገለጸ!

የኢራን መንግስት በሆርሙዝ የባህር ስርጥ ስትራቴጂያዊ ደሴቶች ላይ በርካታ ፈጣን የጥቃት ጀልባዎችን በማሰማራት የተቀናጀ “የመንጋ ጥቃት” (Swarm Tactic) ስልትን ተግባራዊ ማድረጉ ተዘገበ።

በእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል (IRGC) ስር የሚመሩት እነዚህ የባህር ኃይል ክፍሎች፣ የተጣሉ የጉዞ ገደቦችን የሚጥሱ የንግድም ሆኑ የጦር መርከቦችን በፍጥነት ለመጥለፍና ለመክበብ በሚያስችል መልኩ በተለያዩ ቁልፍ ስፍራዎች ተሰማርተዋል።

የዚህ ወታደራዊ ስልት ዋነኛ ዓላማ ትናንሽና ከፍተኛ ፍጥነት ያላቸውን ጀልባዎች በመጠቀም፣ በአጭር የጊዜ ገደብ ውስጥ አንዲትን መርከብ ከተለያዩ አቅጣጫዎች በአንድ ጊዜ በመክበብ ስልታዊ ጫና ማሳደርና ለትዕዛዝ ተገዥ ማድረግ እንደሆነ ተመልክቷል።

Address

Adiss Abebe
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Tofik esmael posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Tofik esmael:

Share