18/04/2026
ሱረቱል አንቢያ (87-90)
87. የዓሣውንም ባለቤት (ዩኑስን) ተቆጥቶ በሄደ ጊዜ፤ (ከዓሣ ሆድ በማውጣት) በእርሱ ላይ ፈጽሞ የማንፈርድበት መሆናችንን በጠረጠረ ጊዜ፤ (አስታውስ)። በጨለማዎችም ውስጥ ሆኖ «ከአንተ በቀር ሌላ አምላክ የለም፤ ጥራት ይገባህ፤ እኔ በእርግጥ ከበዳዮች ነበርኩ» በማለት ተጣራ።
88. ለእርሱም ጥሪውን መለስንለት፤ ከጭንቅም አዳንነው፤ እንደዚሁም አማኞችን እናድናለን።
89. ዘካርያስንም «ጌታዬ ሆይ! ብቻዬን አትተወኝ፤ አንተም ከወራሾች ሁሉ በላጭ ነህ» በማለት ጌታውን በተጣራ ጊዜ (አስታውስ)።
90. ለእርሱም ጥሪውን መለስንለት፤ ለእርሱም የሕያን ሰጠነው፤ ሚስቱንም (መካን የነበረችውን) አበጀንለት (እንድትወልድ አደረግን)። እነርሱ (ነቢያቱ) በበጎ ሥራዎች የሚቻኮሉ፣ ከጅለውና ፈርተውም የሚለምኑን ነበሩ፤ ለእኛም ትሑቶች ነበሩ።
ይህ የቁርአን አንቀጽ በተለይ በችግርና በጭንቅ ጊዜ ወደ ፈጣሪ መመለስንና እርሱም ጸሎትን ሰሚ መሆኑን የሚያሳይ ጥልቅ መልዕክት አለው።