28/04/2025
ከስልጤ ዞን አስተዳደር የተሰጠ የሀዘን መግለጫ
የቀድሞው የስልጤ ዞን አስተዳዳሪና በአሁኑ ሰዓት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ የነበሩት አቶ አሊ ከድር በዛሬው እለት ማለትም ሚያዚያ 20/2017 ኦሮሚያ ክልል ሞጆ የፍጥነት መንገድ ላይ በደረሰባቸው የመኪና አደጋ ህይወታቸው ማለፉ ታውቋል።
አቶ አሊ ከድር ከስልጤ ዞን ምስረታ በኋላ ዞኑን የመሩ ስምንተኛው አስተዳዳሪ የነበሩ ሲሆን በዚህም ከህዳር 2012 እስከ ሀምሌ 2016 ዞኑን በዋና አስተዳዳሪነት መምራታቸው ይታወቃል።
ከሀምሌ 2016 ጀምሮ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ሀላፊ የነበሩት አቶ አሊ በዛሬው እለት በደረሰባቸው የመኪና አደጋ ህይወታቸው በማለፉ የዞኑ አስተዳዳር ጥልቅ ሀዘን የተሰማው መሆኑን እየገለጸ ለዞኑ ህዝብ፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ልባዊ መጽናናትን ይመኛል።