Mereb Cyber Mart - Mereb.com.et

Mereb Cyber Mart - Mereb.com.et Online store for Ethiopian Books, Music, Songs, Movies & more by Ethiopian authors, musicians and film makers. Always!

The Gift Center gives you also an opportunity to leave impression with lasting memories that will make them remembers you!

ለጋዳፊ ሆስተስነት ምልመላ"....እንዳይደርስ የለም ሰዓቱ ደረሰ፡፤ከምሽቱ ሶስት ሰአት ላይ 35 የምንሆን ቆነጃጅት ሸራተን ተገኘን። አብረውን ሶስት ሴት ጋዜጠኞች ነበሩ።ከኔ ጋር የነበሩት ተ...
25/01/2014

ለጋዳፊ ሆስተስነት ምልመላ
"....እንዳይደርስ የለም ሰዓቱ ደረሰ፡፤ከምሽቱ ሶስት ሰአት ላይ 35 የምንሆን ቆነጃጅት ሸራተን ተገኘን። አብረውን ሶስት ሴት ጋዜጠኞች ነበሩ።ከኔ ጋር የነበሩት ተመልማዮች አብዛኞቹ ከገጽታቸው የኮሌጅና የዩኒቨርሲቲ ትምህርት የቀሰሙ ይመስላሉ።ሴቶቹ ከዚህ በላይ እንዳይበዙ በልቤ ተመኘሁ።ጥቂት በኔ ደረጃ ውብ የሆኑ ሴቶችንም ብ እርቀት ተመልክቻለሁ።ኩሪፍቱ ገስት ሀውስ ውስጥ ከነበርነው ሴቶች ውስጥ ክልሷ ልጅ ስትቀር ሁሉንም አየኋቸው።ሶስና በጥግ በኩል ተቀምጣለች።ሲበዛ ሜካፕ ተለቅልቃለች።የምር ቆንጆ ቆንጆ ልጆች ተመልምለው መጥተዋል።ይህንን ሁሉ ምልመላ ያካሄደው ኡስማን ብቻ ነው ብዬ ለማለት ከበደኝ።ብዙም ሳንቆይ አንዲት ሴት እየመራች ጋዳፊ ወዳረፉበት ቪላ ወሰደችን።ሴትየዋን የሆነ ቦታ አውቃታለሁ።ሆኖም ግን ማስታወስ አቃተኝ።በኋላ ላይ ሸራተን ሎቢ ውስጥ ጄነራሉን ስጠብቀው መጥታ ያናገረችኝ ሊቢያዊት እንደሆነች አስታወስኩ።ዛሬ የወታደር መለዮ ለብሳለች።ገዘፍ ያለች ሆና ጠየም ያለች አረብ ናት፤አብራት የሆነሽ ጠብደል ጥቁር ሴት አለች።ይቺ ደግሞ ያው ጋዳፊ እንደ ቻድ ካሉ የአፍሪካ ሃገራት አመቷት ድንግል አጃቢያቸው ትሆናለች ብዬ አሰብኩ።እንግሊዘኛዋ ሲበዛ ቀሽም የሚባል አይነት ነው፤በቅርብ ርቀት ጋዳፊ ካረፉበት ቪላ(Deluxe room/Luxury Villa) የሊቢያ ሰንደቅ አላማ (ባንዲራ) ተሰቅሎ ሳይ ባለሁለት ፎቁ ቪላው ውስጥ ጋዳፊ ያረፉበት መሆኑን ለማረጋገጥ ቻልኩ።"

"...... ቪላው በራፍ ግ ስንደርስ የተወሰኑት የጋዳፊ ደናግላን ሴት አጃቢዎቹ ተከፋፍለው ፈተሹን፤ሁሉም ከወታደራዊው ቆባቸው፣ሚሊተሪ የደንብ ልብሳቸው እና ጉልበታቸው ድረስ የሚደርስ ቡትስ ጫማቸው ጋር ያስፈራሉ።ድንግል መሆናቸውን ሳስብ ግን ሳቄ መጣ።ወደ ውስጥ ዘለቅን፤ሁለቱ ፕሮቶኮሎች ተከፋፍለው 17 የምንሆነውን ወደ አንድ ክፍል ወሰዱን።ወደ መኝታ ክፍል ነበር የሚወስዱን እጅግ ውብ ነው።የጋዳፊ መኝታ ሊሆን እንደሚችል ጠረጠርኩ፣ሁላችንም ደንግጠናል፣በውስጣችን ብዙ ጥያቄዎች ይርመሰመሳሉ፣አንዷ ልጅ በግልጽ በአማርኛ ቅሬታዋን ገለፀች።"

"......ጋዳፊ ወዳለንበት ድንኳን ዘለቁ።ነጭ ጀለቢያና ጥቁር ባለቆዳ ስሊፐር ተጫምተዋል።ጥቁር የበደዊን ጎሳ ይጭንቅላት ጥምጣማቸው እንዳለ ነው። በቴሌቪዢን ከማውቃቸው የበለጠ ገዝፈው ታዩኝ።መጠበቅ ሰልችቶን የተቀመጥን ሁላ ልክ እሳቸው ሲገቡ ተነሳን፤........."

"...ጋዳፊ ሰኞና ሐሙስ በግል ክፍላቸው ውስጥ የተገለጠችን ሴት አያናግሩም፤ሂጃብ ልበሺ!ማስቲካ የምታኝክ ሴት ይጸየፋሉ...ማስቲካ ከያዝሽ ካሁኑ ጣይው...እሳቸው ሳይፈቅዱ እጃቸውን ለመጨበጥ እንዳትሞክሪ.. ምናልባት ካስነጠሰሽ አፍሽን በመሐረብ ሸፍኚ፣ምግብ ከቀረብ እሳቸው ሳይጀምሩ እንዳትጀምሪ... ሺ ማስጠኝቀቂያዎችን ዘረዘረችልኝ።ፈራሁ።..."

ሮዛ ይድነቃቸው

አንድ አዳር ከእትዬ ለምለም ጋርሀሁ ABCD -ይግባኝ ጀመርኩኝእትዬ ለምለምን-ስለተዋወቁኝየምን ቀለም ብቻ-ፊደልን ቆጠራአስተምራኛለች-የአልጋም ላይ ጭፈራ" .....አንገቴን ሳብ አድርጋ ከንፈ...
06/09/2013

አንድ አዳር ከእትዬ ለምለም ጋር

ሀሁ ABCD -ይግባኝ ጀመርኩኝ
እትዬ ለምለምን-ስለተዋወቁኝ
የምን ቀለም ብቻ-ፊደልን ቆጠራ
አስተምራኛለች-የአልጋም ላይ ጭፈራ
" .....አንገቴን ሳብ አድርጋ ከንፈሬን ጎረሰችው።እኔም በስሜት መጠመጥኳት።እጇ በጀርባዬ ይንከላወሳል።እጄን ስባ አንገቷን ፀጉሯንና ጡቷን እንዳሽላት መራችኝ።
የሷ እጅ ከጀርባዬ በጭኔ ስር መዳሰስ ያዘ።ብልቴን ጨበጠችው።የብልቴን ቃጭሎች እንደጭኖቼ ዳሰሰቻቸው።መላ ሰውነቴ በጋለ ስሜት ተናወጠ።
ከንፈሬን አፍንጫዬንና ዓይኔን ብላ አንገቴን ስትስመኝ ነፍሴ ጥላኝ የበረረች መሰለኝ።ትንፋሼ ቀጥ ልትል ስትል ቀና አልኩ።
እንደቀጋ ፍሬ የቀላውን ከንፈሯን እጆቼ አሽቶ አሽቶ እንኩይ ያስመሰላቸውን ጡቶቿን ሳይ"ልዕልት" እንጂ አስተማሪዬ እትዬ ለምለም አልመሰልህ አለችኝ።ሰርጎድ ያለው ሆዷን ገርመም አርጌ አይቼ የተከፈተውን የጭኗን ስር ልዩ ነገር ቃኘሁት"የጅን አረቄው" ሞቅታዬ ተጨምሮበት ዛጎል የማየት ፍላጎቴ ታክሎበት ዘና ብሎ የተከፈተውን የእትዬ ለምለምን ጭን ሳይ ሁለመናዬ እሳት ሆነ።
በእሷ አጠራር ልጠቀምና የእትዬ ለምለም "ሙዳይ" በጥንቃቄ የተላጨ ጋሜ ምስሏል።እንደ አናቴ ፀጉር ይበዛል ያልኩት ጭገር በጎበዝ ገበሬ የተዘራ የጤፍ ማሳ መስሏል።አሳሳኝና በእጄ ነካሁት።አቤት ልስላሴው!የድመታችን ፀጉር ይመስላል።ስልምልም ብላ አየችኝና እጆቼን ጭኖቿን እንዳሻሻቸው አስነካችኝ።ዳበስ----ዳሰስ--እ-ሽ-ት አደረኩላትጭኗን።ጠቁነጠነጠች።ሲብስባት በእግሮቿ ቆለፈችኝና ጭኗ ስር ጣለችኝ።ብልቴ እንደዛሬ ተገትሮ አያውቅም።"ካአፎቱ የተመዘዘ ሳንጃና የተገተረ ብልት አንድ ናቸው።ስጋ ላይ ካልተሰኩ ሸቅሽቀውም ካልወጡ ፋታ አይሰጡም።"እንዳለው ወንድም ጋሼ የተንጋለለችውን ልዕልት ላስገባላት አልኩና ብልቴን ቀሰርኩ።የሙዳይዋ አፍንጫ የቀንድ አውጣ አንቴና መስሏል።መመኪያዬ የሚያሳሳውን ፀጉር ጥሶ እንዲገባ ፍርክስክስ ብር-ግ-ድ-ግድ አድርጋ ከፈተችልኝ።አናቱን አስገባሁት።የእትዬ ለምለም ብልጥ ጠባብ ነው።እስከወገቡ ለማስገባት ትንሽ ታገልኩ።የትንፋሿ ፍጥነትና ድምፅ ጨመረ።....."

ፌላቶኤል ካሣ

የ1997ቱ ምርጫና ቅርጫ፣ ድልና ሽንፈትኅብረቱን በግድም፣በውድም ፈጠርን።በማግስቱ መኢአድ ማንገራገር ጀመረ።በሰሜን አሜሪካ የመኢአድ ዋና ተወካይ ሆኖ ህብረት እንዲፈጠር በጣም ከለፉ ሰዎች ው...
06/09/2013

የ1997ቱ ምርጫና ቅርጫ፣ ድልና ሽንፈት

ኅብረቱን በግድም፣በውድም ፈጠርን።በማግስቱ መኢአድ ማንገራገር ጀመረ።በሰሜን አሜሪካ የመኢአድ ዋና ተወካይ ሆኖ ህብረት እንዲፈጠር በጣም ከለፉ ሰዎች ውስጥ አንዱ የነበረው አቶ ወንዳዬሁ ካሣ ጭንቀት ውስጥ ገባ።በኢትዮጵያ ውስጥ ካለው አመራር ጋር መስማማት እንደቸገረው በግልጽ ይታይ ነበር።ነፍሱን ይማረውና የሚያስከትለውን አደጋ ወዲያው የተረዳው ዶ/ር መኮንን ቢሻው (ለሀገሩም ሳይበቃ ለስብሰባው እንደሄደ ኣዛው አሜሪካ ነው የሞተው)ጨዋታው እንዳይበላሽ ሀገርና ሕዝብን ማስቀደም አስፈላጊ መሆኑን የሚጠቅስ ደብዳቤ ሀገር ለቀረው የመኢአድ አመራር እንደጻፈ ትዝ ይለኛል።ከወራት በኋላ ኢዴፓም የመኢአድን መንገድ መከተል ጀመረ።አሜሪካ ላይ ዓመታዊ ጉባኤያችንን ስናደርግ ኢዴፓም ለመውጣት እንዳኮበኮበና የኢዴፓ መሪዎች ምክንያት እየፈለጉ ከኢህአፓ መሪዎች ጋርና ከነዶ/ር በየነ ጋር አልስፈላጊ ጭቅጭቆች ውስጥ ገቡ።በኢትዮጵያ የተቃውሞ ፖለቲካ ውስጥ ጥሩ ሰው ነው የምለውን ዶ/ር አድማሱ ገበየሁን ኢዴፓ ትዕግስት እንዲላበስ እንዲያደርግ ለመንኩት።ዶ/ር አድማሱ ልደቱን የቻለ አይመስልም።ጭቁጭቁ ቀጠለ።እነሎሬት ፀጋዬ ግ/መድህንና ኮሎኔል አስናቀ ያደረጉት ሙከራም አልተሳካም።ኢሃዴግ ከህብረት ጋር ለመደራደር ስለጠየቀና እኔም ለተጨማሪ አንድ ዓመት እንድመራ ስለተመረጥኩ ከኢሃዴግ ጋር እንኳን ድርድሩን እስክንጨርስ ኢዴፓ ህብረት ውስጥ እንዲቆይ ልደቱን አጥብቄ ለመንኩት።ልመናዬ ብዙውም አልሰራም።ኢዴፓም ወጣ።ኢዴፓ መውጣት ብቻ ሳይሆን ከነመኢአድና በዛው ሰሞን ከተፈጠሩት ቀስተዳመናና ኢዲሊ ጋር ሌላ ቅንጅት ፈጠረ።በዚህም የተከፋፈለ የተቀዋሚ ኃይል ይዘን በምርጫ 1997 ውስጥ ገባን።..."

ዶ/ር መረራ ጉዲና

....ወደ  መርከቧ  የመድፍና የታንክ ጥይት አዘነበ።ይሁንና መርከቧ በከባድ ፍጥነት ወደ ምፅዋ ወታደራዊ መደብር ወደብ ተጠግታ የጫነቻቸውን ወታደሮች አራገፈችና ወደ ዳህላክ ደሴት ተመለሰች።...
25/06/2013

....ወደ መርከቧ የመድፍና የታንክ ጥይት አዘነበ።ይሁንና መርከቧ በከባድ ፍጥነት ወደ ምፅዋ ወታደራዊ መደብር ወደብ ተጠግታ የጫነቻቸውን ወታደሮች አራገፈችና ወደ ዳህላክ ደሴት ተመለሰች።የሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ጥይትም በመጀመሪያው ዓይነት ሸኛት።ከሠላሣ የ ማያንስ የመድፍ ጥይት ቀይ ባህር ውኃው ላይ በማረፍ ሳይፈነዳ ቀርቷል።መርከቧ በከባድ ፍጥነት በመቅዝፍ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከሻዕቢያ ዕይታና ከባድ መሣሪያው ርቀት ውጭ ለመሆን በመብቃቷ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስባት አመለጠች።
ከመርከቧ የወረዱት ወታደሮች ግን ወደ እሣት የተወረወሩ ያህል ነበር ከመርከቧ ወርደው የምፅዋን ምድር እንደረገጡ ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገቡ።ምፅዋ የነበረው ሠራዊት በየቦታው የወደቁትን የአብዮታዊ ሠራዊት አባላትና የከተማዋን ነዋሪዎች አስክሬን እየሰበሰበ በአንድ ጉድጓድ ከአሥር ያላነሰ አስክሬን ሲቀብር ነበር የደረሱት።
ሁኔታውን ለማጣራት ጊዜ ሳያገኙ ደግሞ ስድስት የሻዕቢያ ከባድ መሣሪያ ጥይቶች በአካባቢያቸው ወድቀው ከመካከላቸው አንድ በመግደል ሦስት አቆሰሉ።በሁሉም ዓይን ላይ የመደናገጥ ስሜት ይነበባል።ሞት ተፈርዶባቸው እንደተላኩ ዓይነት እንጂ ለግዳጅ እንደተላኩ አድርገው አልተቀበሉትም።ድብደባውም ቀጠለ።

ታደሰ ቴሌ ሳልቫኖ

የመፈንቅለ መንግሥቱ ዋዜማ ዕለትብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ነዋይ በዚህ ዕለት አበክረው በተያዘ ፕሮግራም መሠረት በክብር ዘበኛ ጦር 2ኛ ብርጌድ ውስጥ የነበሩትን ሻለቆች በትምህርት ላይ እንዳ...
14/05/2013

የመፈንቅለ መንግሥቱ ዋዜማ ዕለት

ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ነዋይ በዚህ ዕለት አበክረው በተያዘ ፕሮግራም መሠረት በክብር ዘበኛ ጦር 2ኛ ብርጌድ ውስጥ የነበሩትን ሻለቆች በትምህርት ላይ እንዳሉ እየተዘዋወሩ ሲመለከቱና ገለፃም ሲቀበሉ እስከ እኩለ ቀን ውለዋል።ከሰዓት በኋላም ሥራ አድርገውት ያሳለፉት የታዋቂውን አትሌት አበበ በቂላ በሮም ከተማ የማራቶን ባለድል መሆኑን መነሻ በማድረግ ለእርሱ የማዕረግ እድገት በመስጠትና ከእግረኝነት ወደ ሻለቃው ስፖርት ክፍል እንዲዛወር በተዘጋጀው በዓል ላይ በመገኘትና ለአበበ ቢቂላ ማዕረግ በመስጠት፣የሙያ አበል በመፍቀድና ዝውውሩን በፊርማ በማፅደቅ ነበር።
በዚህ ቀን መንግሥቱ ንዋይ በሕይወታቸው እጅግ ወሳኝነት ያለው ታላቅ የአገርና የሕዝብ ጉዳይ ለመወሰን በህሊናቸው ያወጡ ያወርዱ ኖሮ እንድሁ ምንም የሚታወቅ ነገር ስለመኖሩ የተመዘገበ የለም።በዚህ ዕለት ምሽት መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ ያስቡ ነበር? ወይስ ስለመፈልቅለ መንግሥት ምንም አይነት የሕሊና ዝግጂት አልነበራቸውም? እንዲያው ዱብ እዳ ሀሳብ ነበር ጦሩን እንዲያንቀሳቅሱ ያነሳሳቸው? እንዲያው ሐሳቡ ኖሯቸው እንደሆነ ምን ምን ጉዳዮችን ለፈፅሙ የሕሊና ዝግጅት አድረገዋል?ለመሆኑ በጽሑፍ የያዟቸው የሥራ ቅደም ተከተሎች/plan check-list/ እቅድ ነበራቸው? ለሚሉት ጥያቄዎች መልስ የሚሆኑ ጉዳዮች አላገኘሁም።

የዕለቱ አመፁ መጀመር.........

ሻምበል ተስፋዬ ርስቴ

ቀኝ-ጌታ ዮፍታሄ ንጉሤቀኝ-ጌታ ዮፍታሄ ንጉሤ (፲፰፻፺፯ ዓ.ም. በደብረ ኤልያስ ቀበሌ፣ ጎጃም ተወልደው ሰኔ ፴ ቀን በ፲፱፻፴፯ ዓ.ም. አረፉ) ስመ ጥር ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። እኚህ ታላቅ...
10/04/2013

ቀኝ-ጌታ ዮፍታሄ ንጉሤ

ቀኝ-ጌታ ዮፍታሄ ንጉሤ (፲፰፻፺፯ ዓ.ም. በደብረ ኤልያስ ቀበሌ፣ ጎጃም ተወልደው ሰኔ ፴ ቀን በ፲፱፻፴፯ ዓ.ም. አረፉ) ስመ ጥር ኢትዮጵያዊ ደራሲ ነበሩ። እኚህ ታላቅ ደራሲ በርካታ ድርሰቶችን የጻፉ ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች አብዛኛዎቹ ለሕትመት አልበቁም።

የመጀመርያውን የኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙር “ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ በአምላክሽ ኃይል በንጉሥሽ” የሚለውን የደረሱት ቀኝጌታ ዮፍታሔ ንጉሤ፤ ስለአገር ፍቅርና ጀግንነት የሚያወሱ በርካታ ድራማዎችና መዝሙሮችን የደረሱ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል “አፋጀሽኝ”፣ “እለቄጥሩ” ወይም “ጎበዝ አየን” ይገኙበታል፡፡ ከድል በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው ከ፲፱፻፴፭ ዓ/ም እስከ ሕልፈታቸው ድረስ አገልግለዋል። የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር እና የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በመታባበር ጳጉሜ ፪ ቀን ፳፻፬ ዓ/ም በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ የተመረቁትን እና የቀኝ-ጌታ ዮፍታሄ ንጉሤን እንዲሁም የደራስያን፤- ነጋድራስአፈወርቅ ገብረ ኢየሱስ፣ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደ ሥላሴ እና አቶ ተመስገን ገብሬን ምስል የተቀረጸባቸው ቴምብሮችን ገበያ ላይ አውለዋል።

የቀኝ-ጌታ ዮፍታሄ ንጉሤ የድርሰት ሥራዎች

ተአምራዊው ዋሽንት (፲፱፻፳፫ ዓ/ም)
ጎበዝ አየን (፲፱፻፳፰ ዓ.ም.) * ምስክር (፲፱፻፴ ዓ/ም)
ጥቅም ያለበት ጨዋታ (፲፱፻፴፩ ዓ/ም)
ሙሽሪት ሙሽራ
ያማረ ምላሽ
የሆድ አምላኩ ቅጣት (፲፱፻፴፪ ዓ/ም)
ዳዲ ቱራ (፲፱፻፴፫ ዓ/ም)
የህዝብ ጸጸት (፲፱፻፴፬ ዓ/ም)
ሙሾ በከንቱ (፲፱፻፴፭ ዓ/ም)
አባት ንጉሳችን ጠረፍ ይጠብቅ (፲፱፻፴፭ ዓ/ም)
የደንቆሮዎች ቲያትር (፲፱፻፴፮ ዓ/ም)
አፋጀሽኝ (፲፱፻፴፮ ዓ/ም)
ዓለም አታላይ (፲፱፻፵፩ ዓ/ም)
እያዩ ማዘን (፲፱፻፵፪ ዓ/ም)
ንጉሡ እና ዘውዱ (፲፱፻፵፮ ዓ/ም)

ምንጭ የጽሀፊ ትዕዛዝ አክሊሉ የፌስ ቡክ ገጽ

Yohannes Admasu

An eighteen-year old girl sets out to meet a young man whom she had never met before and is swept away by a series of ev...
09/04/2013

An eighteen-year old girl sets out to meet a young man whom she had never met before and is swept away by a series of events that transformed her life in a way she could have never imagined. Tower in the sky is the story of love, revolution, hopes, dreams, violence, terror, trust, betrayal, tragedy, disillusionment, self-transformation and the triumphal power of the human spirit. The book vividly depicts a moment in Ethiopia's history when the country convulsed with violence unleashed by a bloodthirsty military government that massacred an untold number of people, especially the young and plunged the country into darkness. It is also the story of thousands of young people who stood up against one of the most brutal dictatorships in history and fought for equality, freedom, social justice and human dignity.

***********************************************
"........The author wrote in detail particularly on Getachew Maru’s role pre and during 1974 revolution period. She loved him dearly as her boyfriend and comrade. She described him as genuine revolutionary, very serious and disciplined, believe in open free discussion to resolve political issues. He was valedictorian student prior joining the university and he continued to be outstanding student in the University. He was well read on communist and socialist theories. Although through out the book, the author shows extreme caution not to fault EPRP, probably due to her love of the party. Reading this book, tells clearly that the political turmoil that created a faction within the EPRP, the debilitating conflict with Mesion and other radical organizations was tragic for young Ethiopians revolutionaries. The harsh methods used to quash dissent within the party, the party major setbacks, and unsuccessful regrouping efforts in cities are also described in this book. The author attempts to uncover her defiance against the military government, and unimaginable price paid by Ethiopian people, and a commitment to serve her party is clearly stated. The author’s observation to some extent is similar to others. Urban armed struggle was intended to conduct as a limited self-defense in the cities but it spontaneously changed to urban style war to defeat the Derg. Hiwot has made an important contribution to the history of unfinished Ethiopian politics" Part of Review by Ewnetu Sime

Hiwot Teffera

Track Listing:Song Title1. Nefsen Yemiyareka (ነፍሴን የሚያረካ)2. Beyet Hager new Egziabher (በየት ሀገር ነው እግዚአብሔር)3. Ejig Yemiya...
12/03/2013

Track Listing:
Song Title
1. Nefsen Yemiyareka (ነፍሴን የሚያረካ)
2. Beyet Hager new Egziabher (በየት ሀገር ነው እግዚአብሔር)
3. Ejig Yemiyamir (እጅግ የሚያምር)
4. sirah Girum ena Dinik New (ስራህ ግሩም እና ድንቅ ነው)
5. Ante Melkam Neh (አንተ መልካም ነህ)
6. Gid Yelem (ግድ የለም)
7. Egziabhier Alelign (እግዚአብሔር አለልኝ)
8. Tilik Neh (ትልቅ ነህ)
9. Kidus Kidus (ቅዱስ ቅዱስ)
10. YaleMihiretih (ያለምሕረትህ)
11. Enenja (እኔንጃ)

ቃልኪዳን ጥላሁን(ሊሊ)

ኢሉሚናቲ በኢትዮጵያ ተረት እና እውነትበአሁኑ ወቅት በሃገራችን ስለ ኢሉሚናቲ  ማወራት ከዓመት በፊት ከነበረው ሁኔታ እንኳ በእጅጉ ተቀይሯል።አሁን ቢያንስ ስሙን እንኳ የሚያውቀው ሰው ቁጥር ...
06/03/2013

ኢሉሚናቲ በኢትዮጵያ ተረት እና እውነት

በአሁኑ ወቅት በሃገራችን ስለ ኢሉሚናቲ ማወራት ከዓመት በፊት ከነበረው ሁኔታ እንኳ በእጅጉ ተቀይሯል።አሁን ቢያንስ ስሙን እንኳ የሚያውቀው ሰው ቁጥር እጅግ በዝቷል።ሆኖም ግን አሁንም ስለ ኢሉሚናቲ ምንነት የጠራ ወይም በነባራዊው የአለም ኢኮኖሚያዊ፣ፖለቲካዊ እና ሃይማኖታዊ መድረክ ዙሪያ ያለውን ወይም የሌለውን ሚና በቅጡ መረዳት ላይ አልተደረሰም።በዚህ ጽሁፍ በተለይ በሃገራችን ላይ አትኩሮት በማድረግ ትክክለኛ የምርምች መርህ ተጠቅመን ስውሮቹን እጆች ለመዳበስ እንሞክራለን።
መጀመሪያ ደረጃ እስካሁን ባለኝ ውሱን መረጃ መሰረት በቀጥታ የኢሉሚናቲ ተፅእኖ ወይም ሙሉ ቁጥጥር የለም የሚለው ድምዳሜ ላይ እንዳለሁኝ ማሳወቅ እፈልጋለሁ።ሆኖም ግን በተዘዋዋሪ ዓለሙን ሁሉ እንደሚቆጣጠሩት ኢትዮጵያም ከዚህ ውጪ እንዳልሆነች የሚያሳዩ ፍንጮች አሉ።ይህም ከኢትዮጵያ አብዮታዊ ንቅናቄዎች ጋር ይበልጡኑ ይተሳሰራል።ዘውዳዊው አገዛዞቹ ከዚህ ቀጥተኛ ያልሆነ የር እዮተ ዓለም የሚያመጣው እስር ነጻ ነበሩ፤ሆኖም ግን ሃይማኖታዊ ሚስጥራት ጋር በተያያዘ ንክኪ ሊፈጥሩ ይችላሉ።
አሁን ከስር የማቀርብላችሁ ምልክቶች በእርግጥም እሉሚናቲ ኢትዮጵያን ሲገዛ ነበር ብሎ አስረግጦ የሚያሳይ ማስረጃ አይደለም።ገፋ ቢል ሊጠቁመን የሚችለው የኢሉሚናቲ ስውር እጆች ከበስተጀርባ እንደነበሩ ነው።ለዚህም ዋና ምክንያት የሚሆነው በመንግስታት ደረጃ ቅድሚያ ከዓለም አቀፋዊነት ይልቅ ብሄራዊነትን የሚያስቀድሙ ፖሊሲዎች የሚያራምዱ በመሆናቸው ነው፤ኢሉሚናቲ ደግሞ በተቻለ ፍጥነት ዓለም አቀፋዊነትን እንዲከተሉ ይፈልጋል።አሁን ወደ ፍተሻችን እንግባ።.....

የላሊበላ ስልጣኔ እና የቴምፕላሮች እጅ?......

ቀዳማዊ ኃይለስላሴ እና ኢሉሚናቲ?......

ድህረ-ነገስታት ኢትዮጵያ እና ኢሉሚናቲ?.........

የችቦ ምልክቶች በሃገራችን........

አሁን የኢትዮጵያ አርማ የሆነውና ባንዲራው መሃል ላይ ያለው ኮከብም ልክ በወታደራዊው ደርግ ጊዜ እንደታየው አንድ አይና ምልክት ወጣ ያለ ነው።ይህም ኮከቡ በተጠላለፉ ዘንጎች የተሰራ መሆኑ ነው።ዘንጎቹ ሲጠላለፉ ለየት ያለ ትርጉም ስለሚሰቱ ነው።እኒሁም የሚያንፀባርቅ መሆኑ ከንጋት ብርሃን እየተባለ ከሚሞካሰው ጋር ሊያያዝ ይችላል......

ግደይ ገብረኪዳን

JANO-An Ethiopian rock explosion melodies,massive bass and drum poly rhythms,metal guitar assault,soaring vocals,dense e...
12/02/2013

JANO-An Ethiopian rock explosion melodies,massive bass and drum poly rhythms,metal guitar assault,soaring vocals,dense electronic textures.

A devastating energy blast!so far, there has been nothing this powerful and versatile that might be associated with "word music"African futurism at its most liberated and intense, a hard rock element unheard of in Ethiopian music,until now,its the New Rock Revolution.

JANO,-The 10 piece Band.ERTALE,the 10 song Release.

The ensemble cast drips with talent.guitarist Michael Hailu supplies the force with huge metal riffs and a detailed harmonic sense.the dual vocals of Debekelu Tafesse and Hailu Amerga are complete contrast with each other.Back and forth,one after another,creating a completely unexpected dynamic that never let's up.

The vision of this music is awe-inspiring.The raw talent,energy and power of the group is overwhelming.it is a musical earth quake the likes of which we haven't seen in generation.the next generation of world music has arrived with a mighty explosion.Stand and behold!

The tracks on JANO's debut release are a tour de force of Ethiopian music reinvented with the intense energy of a rock band and the barley restrained fury of a youth already seeking redemption-a clear parallel to the smoldering volcano in northeast Ethiopia that is namesake for the album,Ertale.

ERTALE -was produced by the legendary producer and musician Bill Laswell who has worked with an extraordinary range of musicians,artists and thinkers around the world.in the Americans Africa,the Caribbean,Europe,the middle East,India,china and Japan.

Jano was created and managed by Trio Entertainment ,which was founded by Addis Gessese (Ziggy Marely,Teddy afro and Gigi) and Ermiyas Amelga,Founder Chairman and CEO of t he Access Group of Companies.Jano is destined to conquer the world.

this is not just an introduction to a new music but to the history of a diverse culture unlike any other.Ethiopia,the only African Country not to be colonized by foreign powers,champions of the battle of Adwa.

Track Listing:
Song Title
1. Ethiopiawit Konjo (ኢትዮጵያዊት ቆንጆ)
2. Yigermal (ይገርማል)
3. Irasen (እራሴን)
4. Ayrak (አይራቅ)
5. Irrekum (እሪኩም)
6. Gude (ጉዴ)
7. Mariye (ማርዬ)
8. Mehed Mehed (መሄድ መሄድ)
9. Tazebkut (ታዘብኩት)
10. Anchi Hagere (አንቺ ሃገሬ)

Ertale (Jano Band): Heleluya Tekletsadik, Hewan Gebrewold, Kirubel Tesfaye, Michael Hailu, Yohannes Mekonen, Debekulu Tafesse, Edward Zekaria, Gemechu Mezgebu, Gudeta Bezabih, Hailu Amerga: Music & Songs / Mezmure

The fascinating biography of Hayla-Sellase I, last Emperor of Ethiopia, who dominated the African and world stage for mu...
21/12/2012

The fascinating biography of Hayla-Sellase I, last Emperor of Ethiopia, who dominated the African and world stage for much of the twentieth century. A thorough and complete portrait, buttressed by rigorous documentary research, but written with the style and pacing of a novel. The author, who is the most respected and well-known historian of Italian colonialism, was an eyewitness to the end of that era, and was personally acquainted with the "King of Kings." The biography includes face-to-face interviews and exclusive documents collected by the author.

ANGELO DEL BOCA

መጣና ጌታችን ላመት ግብራችንሆያ ሆዬ!ሆ!የኔ ጌታ!ሆ!ጌታ ነው ጌታ!ሆ!ጌታ ጠንበለል!ሆ!ዝናቡ መጣ!ሆ!ውዴት ልጠለል!....  ሰኔ ሠላሳ ካለፈ በኋላ የፈተና ውጤታችንን እንዳወቅን ትምህርት ...
04/12/2012

መጣና ጌታችን ላመት ግብራችን

ሆያ ሆዬ!
ሆ!
የኔ ጌታ!
ሆ!
ጌታ ነው ጌታ!
ሆ!
ጌታ ጠንበለል!
ሆ!
ዝናቡ መጣ!
ሆ!
ውዴት ልጠለል!....

ሰኔ ሠላሳ ካለፈ በኋላ የፈተና ውጤታችንን እንዳወቅን ትምህርት ቤታችን ይዘጋል። ሐምሌ ተጠናቆ ታላቅ ፍስሐ ይዞልን የሚመጣው ወር ነሐሴ ነበር። ነሐሴ 13 ቀን ቡሄ ነው። ቀደም ብለን እንዘጋጃለን ።ጅራፍ በሰፈራችን እዚህም እዚያም ይጮሃል።ትልልቅ ሰዎች የትም ሆነው "ኡ! ይጩህባችሁ!..." እያሉ ሲያማርሩ ይሰማሉ። እኛ ግን ትንሽ እራቅ ብለን አካባቢውን በጅራፍ ጩኸት እናደበላልቀዋለን።
ቡድናችን ከዓመት ወደ ዓመት ይለዋወጣል።ቁጥራችን አንዳንዴ ይበዛል፣አልያም ያንሳል።ዘንድሮ እኔ፣ጎቢጥ፣ሙክዬ ቀጫጫው፣ ሲምላል፣ ቅጢሳው፣ ሻቃ ፣ ይጥና ፣ ፕሉቶ፣ ዶሮ፣ ውሮና፣ ጎይቶም አሻሮ የአንድ ቡድን አባል ለመሆን ወሰንን። ዓለምነህንና ወንድሙን ደምስን አናስገባም አልናቸው።ሁለቱ በጉልበት ከእኛ ስለሚበልጡ ዓይን በዓይን ያጭበረብሩናል።ስለምንፈራቸው በዓይናችን ያየነውን ስሙኒ ዲናሬ ነው ሲሉን ማመኑ ለደህንነታችን ይበጃል።አምና የእማማ አመለወርቅ ትልቅ ሙልሙል የት እንዳገቡት ሳይታወቅ ጠፋ።በዚህ ምክንያት ዘንድሮ ከነሱ ጋር ላለመጨፈር ወሰንን።
ዓለምነህና ደምስ በአስተዳደጋቸው እንደኛ በጥብቅ ቁጥጥር ታፍነው ሳይሆን ያደጉት ልቅ ሁነው ነበር።እኛ አጥፍታችኋል ተብለን የምንገረፍበትን ጉዳይ እነሱ አባታቸው ተከራክረውላቸው ነፃ ያደርጓቸዋል።
አንዴ ደምስ እኔን "ገብር" አለኝ። በጉልበት የሚበልጠውን ልጅ የሚያሸንፈውን ልጅ ማስገበር እንደ ደንብ ነበር የምንቆጥረው።ስለዚህ ደምስ ስለሚያሸንፈኝ ቆሎም፣ቂጣም እማዬ ስትሰጠኝ እያመጣሁ እንደገብር አዘዘኝ።ሆያ ሆዬ ሲመጣ ፍራንክ የምገብርበት ጊዜ ደረሰ።እኔ ግን እምቢ አልኩት።በዚህ አመጸኝነቴ መግቢያ መወጫ አሳጣኝ።ሰፈር ውስጥ መጫወትም ሆነ ካምቦሎጆ አካባቢ ዙረት እንዳልሄድ አገደኝ።እኔ ግን እየተደበቁ ሰፈር ውስጥም እጫወታለሁ።ዙረትም እሄዳለሁ።ድንገት ካየሁት እንደ ወፍ ቱር ብዬ እሰወራለሁ።ፀያፍ ስድብ እየሰደበኝ ሲያገኘኝ ደሜን እንደሚጠጣ ይዝትብኛል።
መሸሸጉ ሁሌም አይሞላምና ከካምቦሎጆ ስመለስ መንገድ ላይ ተፋጠጥን።ከአራተኛ ክፍለጦር ፊት ለፊት ነው የተገናኘነው።ወደኋላ ብመለስ ሮጦ ይደርስብኛል።አስጥሉኝ ብዬ የሙጥኝ የምለው ትልቅ ሰው በአካባቢው አጣሁ።ፈትለክ አልኩኝና ባቡር መንገዱን አቋረጥኩኝ።ደምስ ያገኘውን ድንጋይ አንስቶ ወረወረ።እኔን ስቶ የመኪና መስታወት መታ።ባለመኪናው ደምስን ያዙትና ፖሊስ ጣቢያ ወሰዱት።በልጅነት ዘመኔ ደምስ የመጀመሪያ እስረኛ ሲሆን አየሁ።
አባቱ ግን "እንዴት እኔ እያልሁ ልጄን?" ብለው ፎከሩ።ከሳሹንም አሳሪውንም በጆሮ ገብ ድምጻቸው እያቅራሩ አስፈራሯቸው።ሰዎቹ ይቅርታ ጠይቀው ደምስን ለቀቁላቸው።ይህ ድርጊት ከመሰርቱ ሲጠና ጉዳዩ እኔ ላይ አነጣጠረ ቤተሰቦቻችንም በጉዳዩ መክረው ሁለተኛ እንዳይደርስብኝ ታገደ።እኔም ሸክም የወረደልኝ ያህል እፎይ አልኩኝ።ይህ ቂም ስላለብኝ የእኛ የሆያሆዬ ቡድን አባል እንዳይሆን የመጨረሻውን ጥረት አደረኩ።የቡድናችንም አባሎች ድጋፋቸውን ሰጡኝ።
ወንድማማቾቹ የቡድናችንን አባሎች በተናጥል እየጠሩ ያታልሉን ጀመር።እኔ በእንቢታዬ ፀናሁ።ውሮ ግን ለሆያሆዬ እከፍላለሁ ብሎ ከዓለምነህ ስሙኒ ተበድሮ ብይ ተጫውቶ ተበልቷል።ስለዚህ ስሙኒውን እንደሚምረው ሲነግረው ደስ ብሎት እንድናስገባቸው ይለማመጠን ጀመር።በዚህ ተናደን ውሮንም ከቡድናችን አስወጣነው።በጣም አዝኖ እያለቀሰ ለእናቱ እማማ ወርቅውሃ ሄዶ ነገራቸው።
ከእነ ኃይሉ ዶሮ ጋር ጓሮ ጥላው ስር ስር ቁጭ ብለን ስንመካከር እማማ ወርቅውሃ ድንገት ከተፍ አሉ።"እናንተ! እንዴት ብትጠግቡ ነው ልጄን ሆያሆዬ ከእኛ ጋር አትጨፍርም ያላችሁት?"አሉና አፈጠጡብን።'ከልጅ ልጅ ቢለዩ ዓመትም አይቆዩ' ፈሳም ሁሉ!አስገቡት!" ውሳኔያቸውን አሳወቁን።
"እኛ ውሮን እምቢ አላልነውም።እሱ ግን እነ ዓለምነህን አስገቧቸው እያለ ያስቸግረናል።እንቢ ያልነው ለዚያ ነው"አለ ቀጢሳው።
"ውሮ እንደዛ ብለሃል?" ጠየቁ እናቱ።
"አዎን!"
"አንተው ነሃ ጥፋተኛው!እነሱ እኮ ትላልቅ ልጆች ናቸው ያጭበረብሯሽኋል።አንተ ከእኩዮችህ ጋር አርፈህ ተጫወት"መግባባታችንን ሲያዩ ጥቂት ምክር ቢጤ ለግሰውን ጥለውምን ሄዱ።
እነዓለምነህን በተናጠል በመደራደር አልሆን ሲላቸው ወደ ማስፈራራቱ ሄዱ።በዚህ ጥቂት ተሸበርን። ጎቢጥ አንደ አሳብ ትውስ አለችውና እንደ መፍትሄ ለቡድናችን አቀረበ።"ለቦቸራና ለዶጅ ገማጣው ለየአንዳንዳቸው ዲናሬ ዲናሬ ብንሰጣቸው ያስፈራሩናል።እንንገራቸው!"
ማለፊያው መፍትሔ ሆነ።ሁለቱም የመንደራችን ጉልበተኞች "ባትከፍሉንም እንዳይመቷችሁ እናስጠነቅቃቸዋለን"አሉን።ፍራንኩን ግን አይምሩንም።
ከባድ ሸክም የወረደልን ያህል እፎይ አልን።አንደኛው ገንዘብ ያዥ፣ሌላኛው ዳቦ ተሸካሚ በመሆን የጭበረብሩን የነበሩትን ወንድማማቾች በኃያላኑ ኃይል ገታናቸው።ሆኖም ግን ሆያሆዬ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ራሳችንን እንድንጠብቅ መከርን።ለደህንነታችን ሲባል ከመንደራችን አለማራቅ እንደሚበጀን ተመካከርን።
ለችቦ መሥሪያ የሚሆነንን ከሴ መቁረጡን ተውነው።ለምን? ከሴ ቆረጣ ስንሔድ ሁላችንንም ጫካ ውስጥ ይዘው በሳማ ሊገርፉን ወንድማማቾቹ መወሰናቸውን ደረስንበት።ችቦ በዱምብሎ ገዝተን ለማብራት ተመካከርንና ከወጥመዳቸው አመለጥን።
በእቅዳችን መሰረት ጭፈራውን ከእያንዳንዳችን ቤተሰብ እንጀምራለን።እነሱም በደስታ ተቀብለውን ርቀን እንዳንሄድ መክረውን የቻሉትን ይሸልሙናል።ፍራንክም ዳቦም አንድ ላይ የሚሰጡ ቤቶችም ነበሩ።
ወደ ጎረቤቶቻችንና ወደ መንደራችን ሰዎች ቤት ስንዘልቅ ማጣትና ማግኘትን እናስተውል ነበር።አንዳንዶቹ ውስጣቸው በማጣት ጠቁሮ፣እኛ እየጨፈርን ስንመጣ ፈገግ ብለው ይቀበሉናል።ሌሎቹ ደግሞ መጪውን ጊዜ በደስታና በተስፋ ለመቀበል ወስነው ፈካ ብለው ያስተናግዱናል።እጃቸው ቢያጥር እንኳ ለቡና ብለው ያስቀመጧትን እርጋፊ ሣንቲም ይሰጡናል።
የታመሙ ወይም ሥራ ፈት የሆኑ ትልልቅ ስዎች ቤት ጎራ ብለን ጨፍረን በደስታ አድምቀን እንወጣለን።ከልጆቻቸው መረጃ ስለሚደርሰን ዳቦም ሆነ ፍራንክ ከዚያ ቤተሰብ አንጠብቅም።የእነዝህ ችግረኛ ቤተሰብ ምርቃት አሁንም ትውስ ይለኛል።"እግዜር ያሳድጋችሁ!እሱ ወሮታውን ይክፈላችሁ!ከዓመት ወደ ዓመት አብረን እንደንሸጋገር፣የደስታችሁ ተካፋይ ልታደርጉኝ መጣቹህ? እኔን ለወግ ለማዕረግ እንዳበቃችሁኝ እሱ አይመርምሬው እናንተን አግኝቶ ከማጣት አይድናችሁ!"
ከእነዚህ ሰዎች አንድዳንዶቹ ክፉ ቀን የሚሉትን አሳልፈው፣ የተሻለ ህይወት በበኋለኛው ጊዜ ይኖራሉ።በዚህ ወቅት እኔ ም ሆንኩኝ አብሮ አደጎቼ ጎርምሰናል።ያኔ ቤታቸው ሄደን ሆያሆዬ የጨፈርንላቸውን ከውለታ ቆጥረው ለወላጆቻችን ማጫወታቸውን አስታውሳለሁ።
ስንጨፍር በደንብ ግጥም ማውረድ በማይችል ልጅ ስህተት ቅር የተሰኘ ቤተሰብ ከእኛ ውትወታ የሚገላገልበት ወቅትም ነበር።
"ሆያሆዬ ብሯን ብሯን ይላል ሆዴ!"ሲልና እኛ ስንቀበል፣
"ኧረ!ብሯን ብሯን አለ ሆድህ!?"ይላሉ
"ሆያሆዬ ና! ና! ልምጣ ወይ ወደ ማታ!"
"አሁን ገና አወቃችሁልኝ! አዎን ወደ ማታ ኑ!" ይሉናል......

****************************************
በዚያ የለጋነት ዕድሜ ገንዘብ ይዞ መገኘትበወላጆቻችን ስለሚያስቀጣ የደረሰን ዲናሬ እንደሆነ አስረድተን ለቡና ማፍያ እንዲሆናቸው ለእናቶቻችን እንሰጣቸዋለን።የአንዳንዶቻችን ወላጆች ከፈቀዱልን ፓስቴ እንገምጥበታለን።ሽልንጋችንን ግን በተለያዩ ቦታዎች እንደብቃለን።እኔ በቁምጣ ሱሪዬ ውገብ ላይ ያለውን ድርብ ጨርቅ ቀድጄ ምስጢር ኪስ ስለሰራሁ እዚያ ወስጥ ደበቁት።መሰለ ዲዲ አባባ ዘውዴ ግቢ ሠንሠሉ ውስጥ ጉድጓድ ቆፍሮ ፍራንኩን ቀብሮ ለምልክት እላዩ ላይ አሩን አራበት።ሲምላል ሽንቱን በጊዜ ሸንቶ ወሸላው ሸለፈት ውስጥ ከትቶ በክር ሸብ አድርጎት አደረ።ቀጢሳው ፍራንኩን የት እንደሚደብቅ እስካሁን አላወቁም።መኩዬ ቀጫጫዋ ግን ወንድምዋ ኪሷን ፈትሾ እንዳይሰርቃት በመስጋት ለሚፈራት ልጅ ደብቅልኝ ብላ አደራ ትሰጠዋለች።...የዚያን ዕለት ለደንቡ ያህል ሁላችንም ቤታችን ገብተን እንጋደማለን እንጂ እንቅልፍ በዓይናችን ሳይዞር ይነጋልናል።

ዘነበ ወላ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mereb Cyber Mart - Mereb.com.et posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Mereb Cyber Mart - Mereb.com.et:

Share

Category